Thursday, 19 May 2016

ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊው ሊቅ

 ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊው ሊቅ
መግቢያ
መላእክት ምስጋናቸው እረፍታቸው ፣ እረፍታቸው ምስጋናቸው ሆኖ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ እግዚአብሔርን ያለማቋረጥ ያመሰግናሉ፡፡ ቤተክስቲያንም አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድረግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት የሚመሰገንበትን የምስጋና ሥርዓት ዘርግታለች፡፡
ሕያው እግዚአብሔር የአዳም ልጆች በመላእክት ምስጋና እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምጋና ይማር ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መረጠ፡፡

• ቅዱስ ያሬድ ኢትዮጵያዊው ሊቅ
ቅዱስ ያሬድ ሚያዝያ 5 ቀን 505 ዓ.ም አክሱም ከተማ ተወለደ፡፡ ያሬድ ማለት መውረድ ማለት ነው ፡፡ ሰማያዊውን ጣእመ ዜማ ወደ እኛ የሚያወርድ ነውና፡፡
‹‹ዋይ ዜማ!!! ዘሰማዕኩ እመላእክት ቅዱሳን ›› ‹‹ ከሰማይ ከቅዱሳን መላእክት የሚያስደንቅ ዜማ ሰማሁ›› በማለት እንደተናገረ በአክሱም መጻሕፍትን እያስተማረ ሳለ ከሰማያውያን መላእክት ጣእመ ዜማን ተማረ፡፡ በተመስጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ተነጠቀ፡፡ በዚያም መላእክት ልዩ ጣእም ባለው የዜማ ድምፅ ሊያመሰግኑ ሲዘምሩና ሲያሸበሽቡ አየ፡፡ ከጣዕመ ዜማውም የተነሣ ተደነቀ፡፡ የእግዚአብሔርን ስም እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስን በጠራ ጊዜ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ዜማ ተገለጸለት፡፡ ተመልሶም ወደ ምሥራቅ ዞሮ እጁንም ዘርግቶ ‹‹ ሃሌ ሉያ ለአብ ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ ፣ ሃሌሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን . . . ›› ብሎ በአክሱም ከተማ ሙራደ ቃል /የቃል መውረጃ/ በተባለችው ሥፍራ ለመጀመሪያ ጊዜ ዜማን በዐውደ ምሕረት ያሰማ የዜማ ደራሲ ነው፡፡
• የቅዱስ ያሬድ አስተዋጽኦ
ዓለም ከሚያውቃቸው የዜማ ደራስያን ከሞዛርትና ከሌሎችም አስቀድሞ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ እዝልና አራራይ በተሰኙ የዜማ ስልቶች የማይሰለችና ዘመን ተሸጋሪ ዜማን፣ የዜማ ምልክቶችንና የተለያዩ ድርሰቶችን በመድረስ ሃገራችን የዚህ ታላቅ መንፈሳዊ ሀብት ባለቤት እድትሆን አድርጓል፡፡
ቅዱስ ያሬድ በሰዓታት ፣በወራትና በዘመናት የተከፋፈሉ ድንቅ ምስጋናዎችን ከብሉያትና ከሐዲሳት ንባብና ምሥጢር ለቤተክርስቲያን እንደ ሰምና ወርቅ አስማምቶ የአገልግሎት ሥርዓትን የሠራ የቤተ ክርስቲያን አምድ ነው፡፡
የቅዱስ ያሬድ ዜማ ድንቅና ጥልቅ የነገረ ሃይማኖት አስተምህሮት ፣ የቅዱሳት መጻሕፍን ንባብ ትርጓሜ እንዲሁም የታሪክ ምስክርነትን የያዘ ከፍ ያለ ዋጋ ያለው ድርሰት ነው፡፡
ቅዱስ ያሬድ ዛሬ በጉባኤ ቤት ለዜማ ትምህርት ቤተክርስቲያን የምትገለገልበትን ሥርዓተ ትምህርትና የመማሪያ መጻሕፍትን የደረሰ ሊቅ ነው፡፡ ድረሰቶቹም ምዕራፍ ፣ጾመ ድጓ፣ ዝማሬና መዋሥዕት ይባላሉ፡፡
ቅዱስ ያሬድ በአክሱም በመምህሩ በጌዴዎን ወንበር ተተክቶ መጻሕፍተ ብሉያትና ሐዲሳትን አስተምሯል፡፡ ከአቡነ አረጋዊና ከአፄ ገብረ መስቀል ጋርም በመሆን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎት በጣና ቂርቆስ ፣በዙር አባ አቡነ አረጋዊ ገዳም እንዲሁም ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እስከ ብርብር ማርያም በመሄድ ያስተማረ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡
አጠቃላይ በሥነ ጽሑፍና በቋንቋ እድገት በነገረ መለኮትና በታሪክ ትምህርት እንዲሁም በሥርዓተ ጸሎት የቤተ ክርስቲያን አንድነት በማስጠበቅ ረገድ ጽኑ መሠረትን የጣሰ ታላቅ ሊቅ ነው፡፡
• የቅዱስ ያሬድ ምናኔ
ቅዱስ ያሬድ የሕይወት ዘመኑን በጸሎትና በብሕትውና ለማሳለፍ ወደ ሰሜን ተራራ ምድረ ጸለምት በመሄድ /በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በበየዳ ወረዳ በሚገኝ ሥፍራ/ ብርድ በጸናበት በረዶ በሚፈላበት በሐዊ ተራራ በጽሙና ተቀምጧል፡፡ በዚያም ጉባኤ ዘርግቶ ትምህርት አስፋፍቶ ለሃያ ሁለት ዓመታት አስተምሯል፡፡
ቅዱስ ያሬድ ዘመኑን ሁሉ በማኅሌት እግዚአብሔርን በማገልገል በጣእመ ዜማው ዲያብስን ድል መትቶ በዚያው በሐዊ ተራራ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ ገብቶ ግንቦት 11 ቀን በሰባ አምስት ዓመቱ ከዚህ ዓለም ውጣ ውረድ ተለይቷል፡፡ ቤተክርስቲያንም ቅድስናውንና አማላጅነቱን አምና በስሙ ጽሌ ቀርጻ፣ ቤተክርስቲያን አንጻ ፣ ድርስቶቹንም የቤተክርስቲያን መገልገያና የስርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ አድርጋ እየተጠቀመችባቸው ተገኛለች፡፡
በምናኔ በኖረበት ሥፍራም በስሙ ገዳም ተገድሞ መናንያን አሰረ ፍኖቱን ተከትለው ጤዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው፣ በረዶውንና ውርጩን ታግሠው በስሙ እየተማጸኑ ይኖራሉ፡

የቅዱስ ያሬድ የዜማ ዓይነቶች 3ት ናቸው፡፡ እነርሱም ግእዝ፣ዕዝልና አራራይ  በመባል ይጠራሉ፡፡ ሦስቱም የዜማ ዓይነቶች ምን ጊዜም ሕያዋን ሆነው በቤተክርስቲያን ሰፊ የአገልግሎት ድርሻ አላቸው፡፡ ሦስቱም ዜማዎች መጽሓፍ ቅዱሳዊ ምሳሌና ትርጉም አላቸው የዜማዎቹ ሦስትነት የምሥጢረ ሥላሴ ምሳሌ ሲሆኑ ለአንድ አገልግሎት /ምስጋና/ መዋላቸው ደግሞ የሥላሴን አንድነት ያስረዳል፡፡

ይህም ሲተረጎም፡-
  • ግእዝ ማለት በመጀመሪያ የተገኘ ማለት ነው፡፡ የቃሉ ትርጓሜም ‹‹ገአዘ›› ነጻ ወጣ ማለት ሲሆን በዜማነቱ ሲተረጎም ስልቱ የቀና ርቱዕ ቀጥ ያለ ጠንካራ ማለት ይሆናል፡፡ ምሳሌነቱም የአብ ሲሆን ከዜማው ጠንካራነት የተነሳ ሊቃንቱ ደረቅ ዜማ ብለውታል፡፡
  • ዕዝል፡- ከግእዝ ጋር ተደርቦ ወይም ታዝሎ የሚዜም ለስላሳ ዜማ ነው ዕዝል ጽኑዕ ዜማ ማለት ሲሆን በወልድ ይመሰላል፡፡ ምክንያቱም ወልድ ጽኑዕ መከራን ተቀብሏልና፡፡
  • አራራይ፡- የሚያራራ የሚያሳዝንና ልብን የሚመስጥ ቀጠን ያለ ዜማ ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ ይመሰላል፡፡ ሐዋርያትን ከበዓለ ጰንጠቆስጤ /ከበዓለ ጰራቅሊጦስ/ በኋላ ያረጋጋ፣ ያጽናና እና ጥብዓት /ጽፍረት/ የሰጣቸው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና፡፡የሐዋ. 2፤1 ዮሐ.15 26 ፡፡
በቤተክስቲያን የሚቀርበው ምስጋና በሙሉ በሦስቱ የዜማ ዓይነቶች  ነው ከዚህ የሚወጣ ዜማ ያለው ዝማሬ በቤተክርስቲያን የለም ቢኖርም የቤተክርስቲያን አይደለም፡፡ ማንኛውም ሰው በቤተክርስቲያን መዝሙር የሚያቀርበው የቅዱስ ያሬድ የዜማ ምልክቶችና ዓይነቶች ተከትሎ ነው፡፡ ከሦስቱም የዜማ ዓይነቶች የወጣ ዜማ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም ሦስቱም የዜማ ዓይነቶች ራሳቸውን ችለው የሚዜሙ ቢሆኑም አንዱ የዜማ ዓይነት በሌላው የዜማ ዓይነት ውስጥ የሚገኝ መሆኑን መታወቅ አለበት፡፡ ለምሳሌ ያህል በግእዝ የዜማ ዓይነት የአራራይ ዜማ ይገኛል፡፡ ይህ ሲባል ግን አንዱ ሌላውን ይተካል ማለት ሳይሆን አንዱን የዜማ ዓይነት በሌላው የዜማ ዓይነት ውስጥ በተወሰነ መጠን ተመሳስሎ ይገኛል ለማለት ነው፡፡ በምሳሌ ለማስረዳት፡- የቅዳሴ፣ የኪዳን፣ የሰዓታት ጸሎት በሦስቱም የዜማ ዓይነቶች የተቀመረ ሆኖ እናገኘዋልን፡፡  አንድን ቃል ወይም ጸሎት በሦስቱም የዜማ ዓይነቶች ማዜም ይቻላል፡፡

Thursday, 12 May 2016

ለእመቤታችን ሥዕል ከነበረው ፍቅር የተነሣ ጽጌረዳ ለሚሰጣት ለዘካርያስ የተደረገ ተአምር

ለእመቤታችን ሥዕል ከነበረው ፍቅር የተነሣ ጽጌረዳ ለሚሰጣት ለዘካርያስ የተደረገ ተአምር

 
 
 
 
 
 
ከሮም ነገሥታት ወገን የሆነ ስሙ ዘካርያስ የሚባል አንድ ጎልማሳ ሰው ነበር፣ ከእለታት አንድ ቀን ከቤተክርስቲያን ገብቶ በእመቤታችን ፊት ሲጸልይ ከሥዕሏ ማማር የተነሳ ደስ አለውና ለዚች ሥዕል ምን ዓይነት እጅ መንሻ ላቅርብላት እያለ ሲያወጣና ሲያወርድ፣ ወራቱ የጽጌሬዳ ወራት ነበርና 50ውን የጽጌሬዳ አበባ ወስዶ ዘውድ አስመስሎና አክሊል ሰርቶ ከሥዕሏ ራስ ላይ በክብር አቀዳጃት፡፡
ይህ ሰው እንደዚህ እያደረገ ሲጸልይ ከቆየ በኋላ፣ የጽጌሬዳ ወራት ባለፈ ጊዜ ግን ለሥዕሏ ክብር የሚያቀርብላት የጽጌሬዳ አበባን በማጣቱ፣ እጅግ አዝኖ ወደ ቤተ-ክርስቲያን ሔደና በሥዕሏ ፊት ቆሞ እመቤቴ ማርያም ሆይ የጽጌሬዳ ወራት እንደላፈ አንቺ ታውቂያለሽና በ50ው የጽጌሬዳ ፋንታ ሰላምታሽን 50 ጊዜ እጸልያለሁ በማለት እንዲህ አለ፣ እመቤቴ ማርያም ሆይ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ ሰላም እልሻለሁ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ እያለ በየቀኑ ሲጸልይ ኖረ፣ ከዕለታት አንድ ቀን ግን ይህችን ጸሎት ሳያደርስ ወደ አንዲት ሀገር ለመሄድ መንገድ ጀመረ።
ሥዕል 18 ኛው መ.ክ.ዘ. የተሠራ የቅድስት ድንግል ማርያም እና ለወዳጇ ዘካርያስ ያደረገቸውን ተአምር የሚያሳይ ሥዕል
ሥዕል 18 ኛው መ.ክ.ዘ. የተሠራ የቅድስት ድንግል ማርያም እና ለወዳጇ ዘካርያስ ያደረገቸውን ተአምር የሚያሳይ ሥዕል
በመንገድም እያለ ይህቺን ጸሎት እንዳላደረሰ አስታውሶ፣ ጉዞውን አቋርጦ ከመንገድ ወጣ ብሎ እንደቀድሞው እየሰገደ ሰላምታዋን ሲጸልይ፣ በእያንዳንዱ ሰላምታ ከአፉ የጽጌሬዳ አበባ ሲወጣና አበባው 50 እስኪሞላ ድረስ፣ የጽጌሬዳውን አበባ እመቤታችን ከአፉ እየተቀበለች በክንዷ ስታቅፍ፣ በአካባቢው የነበረና የሽፍቶች አለቃ የሆነ አንድ ሰው ይህን አይቶ፣ ጸሎቱን እስኪጨርስ ድረስ ከአፉ የሚወጡ ጽጌሬዳዎችን ይቆጥር ጀመረ።
ዘካርያስም ጸሎቱን ሲጨርስና አበባዎች 50 ሲሞሉ እመቤታችን ባርካው ወደሰማይ ስታርግ ይህ የሽፍቶች አለቃ አይቶ፣ እጅግ አደነቀና ጓደኞቹን ጠርቶ የጌታን ተአምር ታዩ ዘንድ ኑ ተብሎ እንደተጻፈ መዝ 45፡8 ልዩ ተአምር ኑ እዩ ብሎ ወደ ዘካርያስ ወሰዳቸው።

http://ethiopianorthodoxmiracles.blogspot.be/search/label/%E1%89%A3%E1%88%95%E1%89%B3%E1%8B%8A%20%E1%8A%A0%E1%89%A3%20%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8%20%E1%8C%8A%E1%8B%AE%E1%88%AD%E1%8C%8A%E1%88%B5

የዝሙት መንፈስ ምንድነው? አይነጥላ ምንድነው?

የዝሙት መንፈስ ምንድነው? አይነጥላ ምንድነው?


ዝሙት  
" የእግዚአብሔር ልጆችና የዲያብሎስ ልጆች በዚህ የተገለጡ ናቸው " 1 ዮሐ, 3 : 10
ለብዙ ዘመን ያህል የካበተ የማሣሣቻ ልምድ ያለውና የሰዎችን መልካም ጠባይ የሚያበላሽው አንዱ የዝሙት መንፈስ ሲሆን ዘወትር እንደ አዲስ ነገር አመልካች በመሆንና ግፈትን በማጠናከር በልብ ውስጥ የሩካቤ ቅስቀሳ በማድረግና ሰዎች ዝሙትን እንደ ተለመደ ኖርማል ነገር አድርገው እንዲወስዲና ድርጊቱን በግልጽ ነውረኝነትና በድፍረት እንዲፈጽሙ ያነሣሣል : : የዝሙት መንፈስ እግዚአብሑር ለሰው ልጆች ከሰጠው የተፈጥሮ ጠባይ በማዛነፍና በማዛባት ቀደም ሲል እንደተጠቀሰው ሰዎችን በማስነወር ለተፈጥሮ ግብር ተቃራኒ በማድረግና በማርከስ ፍጹም የአመንዝራነትና የሴሰኝነትን ሰይጣናዊ ጠባይ ያወርሳል ዛሬ በዓለማችን ላይ ያለው የተራቀቀ ቴክኒዎሎጂ በተለይም የኢንተርኔት አግልግሎት ከሰጠው አዎንታዎ ጥቅም በተጨማሪ በአሉታዊ መልኩ ሰዎች በዝሙት : በኮክብ ቆጠራ : በሥነ ልቦናና : በፍልስፍና ወዘተ . . . መንፈሶች እንዲ ልክፍት ከፍተኛ አስተዋጽፆ አበርክቷል : : " እንግዲህ በምድር ያሉትን ብልቶቻችሁን ግደሉ እነዝህም ዝሙትና ርኩሰት ፍትወትም ክፋ ምኞትም ጣዖትንም ማምለክ የሆነ መጐ ምጀት ነው በእነዚህም ጠንቅ የእግዚአብሔር ቁጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ይመጣል : : "ቄላስይስ. 3 : 5 - 6  

የዝሙት መንፈስ የመግቢያ አቅጣጫዎች -

 አብሮ በሚወለድ አጋንንት ዛር በውርስ መንፈስ በኩል ከሴትዋጋር አብሮ በሚወለድ ወንድ የአጋንንት ዛር በተቃራኒው ደግሞ ከወንዱ ጋር አብራ በምትወለድ ሴት የአጋንት ዛር አማካኝነት - በመተት ለዲያብሎስ ያደሩ ሰዋች ወደ ሌሎች አስመትተው በመላክ - ከዓይን ላይ በሚነሣ መንፈስ (ብዳ) አማካኝነት ከውስጥ ወደ ውጭ በሚያይ የዝሙት መንፈስ ዓይን አማካኝነት የመንፈሱ ስሜት ይገባል : : - በማየት : በማዳመጥ : በማንበብ በኩል የሚገባ የወሲብ ፊልሞችንና ስዕሎችን በማየት ተመሣሣይ ወሲብ ነክ ንግግሮችን በሙሉ ሰሜት በማዳመጥና ጽሁፎችን በማንብ በፊልሙ በንግግሩና በጽሁፉ ላይ በሚናር ሙሉ ተመስጣ ወይም ከፍተኛ ትኩረት የተነሣ የዝሙት መንፈስ ወደ ሰዎች ይገባል : : ከዝህ በተጨማሪ መንፈሱ ከሰፈነበትና የሚውጠውን ለመፈለግ በሚንቀሣቀስበት አየርና መንገድ ላይ ያገኛቸውን ሁሉ ይጠልፋል : : ለዚህ በተለይ ምሳሌ የሚሆኑን በአገራችነ በኑሮና በባህል ተጽዕኖ አስገዳጅት ቺግር የገጠማቸውን አንዳንድ እህቶቻችንን እያሳደደና መጥፏ አማራጭ እያሳያቸው የሴትኛ አድሪነት ሕይወትን እንዲመሩ የመገፋፋቱ ጉዳይ ነው : : የእነዚህ የዝሙት መንፈሶች ተጋቦት ፈጣን በመሆኑ ዱያቢሎስ ስዎቹን ቅብጥብጥ : እፍረተ-ቢስ : ነውረኛ ርካታ-ቢስ ወዘተ. . . በማድረግ በመጨረሻ ሥነ-ምግባራቸውና ግብራቺው ለክርስቲያናዊ ሕይወት የሃይማኖት ቅድስና አደገኛ ይሆናል : : የሩካቤ ክፉ መንፈሶች ከሌሎቹ የጥፋተ መንፈሶች ለየት ባለ መንገድ ብዙ ጠባይ አላቸው : : ከነዚህም ውስጥ ለምሳሌ ሴት አጋንንት ዛር ከውንዱ ጋር አብራ ከተወለደች በእድገቱና በዕድሉ ስለምትቀና ሩካቤውን ለራስዋ በምትፈለልገው መልክ ትቆጣጠራለች : : በዚህ የተነሳ ሰውየውን ዓይነ-አፋር : ፈሪ እና : ድንጉጥ ልታደርገው ትችላለች በሴቷ ውስጥም ያለው ወንድ አጋንንት እንደዚሁ ዓይነት ተመሣሣይ ጠባይ ያሳያል ብዙ ጊዜ ይህ የዝሙት መንፈስ በዛር በኩል ውርስ ሆኖ ሊመጣ ወንዱንም ሆነ ሴቷን ፍጹም ዓይን ወደ አወጣ ሴሰኝነት በታቃራኒው ወደ ዓይነ-አፋርነት በመለወጥ ከፍተኛ አለመግባባት በባልና በሚስት መካከል በመፍጠር የወንዱ ሕይወት በሴቷ የሴቷ ሕይወት ደግሞ ሁለቱንም ጻታዎች ልባቸውን የሩካቤ ስሚታቸወን የሞተ አድርጎ በማሳቀቅ የሚያዝኑና የሚያለቅሱ ብቸኛ ሰው ሆነው የሌሎችን ትዳርና ልጆች ሲያዩ እንዲማረሩ አድርጎ ሕይወታቸውን በራሳቸው እጅ እንዲያሳልፉ ይህ የዛር መንፈስ ግፊት ያደርጋል : : የመንፈሱ ተጽዕኖ እጅግ ከባድና የሰዎች ጠባይ አውሬነት ሁሉ እስከ መለወጥ ያደርሳል ምክንያቱ ደግሞ ተደጋግሞ እንደተገለጸው አብሮ የተወለደው አጋንንት ዛር ሙሉ በሙሉ ከሰዎች ጋር ስለተዋሃደና ቤቱን በላያቸው ላይ ሠርቶ ዘሬናቸው እያለ ስለሚፍክር ነው : : 
 
" ይህን እወቁ አመንዝራም ቢሆን ወይም ርኩስ ወይም የሚመኝ እርሱም ጣዖት የሚያመልክ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መግስት ርስት የለውም " ኤፌ 5 : 5 
የሳጥናኤል ሠራዊት  * ባጀት አይፈልጉም የሚንቀሳቀሱት በአንተ በጀት ነው : : * ቢሯቸው አይዘጋም ምን ጊዜ ምክፍት ነው : : * አያንቀላፉም መዘናጋት በእነርሱ ዘንድ የለም : : * አያረጁም ጡረታ አይወጡም * በፓሊስ አይያዙም በፍርድቤት አይዳኙም * አይቀበሩም ወደ ሲኦል ተሸኝተው ካልታሰሩ በስተቀር አይሞቱም : : 
" የድንግል ማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ከርኩሳን መናፍስትና ከሴሰኝነት ያውጣንና ይጠብቀን " አሜን !

አይነ ጥላ

በማለዳ መያዝ መጽሐፍ ገጽ.57 
አይነ ጥላ በምናየው በምንረዳው በምንገነዘበው ወዘተ..መንገዳችን ላይ አሸምቆና ተደብቆ ጉዳት የሚያደርስብን የሚያርፍብ የክፉውን መንፈስ ጥላ ዋንኛው የዲያብሎስ የጥቃት ክንድ ነው::
የዓይነ ጥላ መንፈስን ልዩ የሚያደርገው በመጀመርያ ደረጃ በውስጣችን ሲገባ ከጠባያችን ጋር መመሳሰል መቻሉ አንዱ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ተምረን ጥረን ግረን የት እንደምንደርስ እንዴት እንደምናድግና ዕድላችን እንዴት እንደሚቃና አስቀድሞ በማወቅና አርቆ የማየት ከፍተኛ ችሎታ ያለው መንፈስ መሆኑ ነው:: .....
ለምሳሌ እንመልከት
ቢሮ ከሆነ አንተ ውስጥ ያለው አይነጥላ  ከአንተው ላይ ተነስቶ አለቃህ ውስጥ ቀድሞ ገብቶ ይጠብቅሃል:: ቢሮ እንደደረስክ ራስህን እስክትጠላ በከባድ ቁጣና ሞራል በሚነካ ዘለፋ ያስተናግድሃል::የሥራህ ሕልውናም ሊያከትም እንደሚችል በመግለጽ ያስፈራራሃል ያስጠነቅቅሃል:: አንተም ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ትጀምራለህ:: ወደ አካል ግጭት ሁሉ ልታመራ ትችላለህ::
ተጨማሪ ያንብቡ...