ቀደም ብለው በገጸ ጦማሬ ከተለጠፉት ጽሑፎች መካከል ያልደረሳቸው ይደርሳቸው ዘንድ . . .
መዝሙር እንዴት ይደመጣል?
ዓባይነህ ካሤ - ዲን
ሰሞኑን አግሮቼ ወደ አንድ ቢሮ ይዘውኝ ገቡ፡፡ በዚያም ቢሮ ውስጥ በርካታ መንፈሳውያን እንዳሉ በሚያረጋግጥ ሁኔታ ከአንድ ኮምፒውተር ላይ አንድ መዝሙር ለስለስ ብሎ ይደመጣል፡፡ ታዲያ እኔም ለመጠየቅ ያኽል የምቀርባቸው ሰዎች ነበሩና ለመኾኑ እያዳመጣችሁት ነው ወይንስ እየሰማችሁት? የሚል ጥያቄ ሰነዘርሁላቸው፡፡ ለካ የሁሉም ጉዳይ ነበረና ሁሉም ስሜቱን መግለጥ ጀመረ፡፡ የሚገርመው መዝሙሩ የሚሰማበት ኮምፒውተር ባለቤት ከፍታው ስለወጣች ውይይቱን የተቀላቀለችው ዘግየት ብላ ነበር፡፡
ሁሉም ሰው በአንድ ነገር ተስማማ፡፡ እርሱም "ባናዳምጠውም የሚያረጋጋ መንፈስ ስለሚፈጥርልን እንዲሁ ስንከፍተው ደስ ይለናል" የሚል ነበር፡፡ እኔም በኩሌን ሀሳብ ሰንዝሬ ተስማምተን ተደማምጠን የሄድሁበትንም ሳልረሳ ወጣሁ፡፡ ነገር ግን ሁልጊዜ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ከዛሬ ነገ ሀሳቤን እሰነዝራለሁ ስል የከረምሁበት አጀንዳ ነበረና የእነዚያ ወንድሞች እና እኅቶች ውይይት የበለጠ አነቃኝ፡፡ እናስ እንዴት መዝሙር ይደመጥ?
ሁሉም ሰው በአንድ ነገር ተስማማ፡፡ እርሱም "ባናዳምጠውም የሚያረጋጋ መንፈስ ስለሚፈጥርልን እንዲሁ ስንከፍተው ደስ ይለናል" የሚል ነበር፡፡ እኔም በኩሌን ሀሳብ ሰንዝሬ ተስማምተን ተደማምጠን የሄድሁበትንም ሳልረሳ ወጣሁ፡፡ ነገር ግን ሁልጊዜ በአእምሮዬ እየተመላለሰ ከዛሬ ነገ ሀሳቤን እሰነዝራለሁ ስል የከረምሁበት አጀንዳ ነበረና የእነዚያ ወንድሞች እና እኅቶች ውይይት የበለጠ አነቃኝ፡፡ እናስ እንዴት መዝሙር ይደመጥ?
ዘመረ አመሰገነ ነው፡፡ ስለዚህም መዝሙር ማለት ምስጋና ማለት ነው፡፡ ምስጋና ማቅረብ ተገቢ ነው፡፡ ምስጋና በዜማ ፣ ምስጋና በጸሎት ፣ ምስጋና በጽሑፍ ፣ ምስጋና በአርምሞ ሊቀርብ የሚችል መሥዋዕት ነው፡፡ መዝሙር ስንል በልቡናችን ሰሌዳ ወለል ብሎ የሚታየን ግን በዜማ የሚደረገው ምስጋና ነው፡፡ ይኽም በዜማ የተዋዛ መዝሙር ምስጋና ብቻ ሳይኾን ጸሎትም ነው፡፡ ጸሎትም ምስጋናን ከልመና ያስተዛዘለ ነው፡፡ ከዚህም አልፎ ትምህርትም ነው፣ ደግሞም ምስክርነት ነው፡፡ ያመንነውን እንናገርበታለንና !
ዛሬ ዘመኑ ፈቀደልንና በድቃቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የፈለግነውን ያኽል ፋይሎች ይዘን በፈለግነው ቦታ ጥቅም ላይ እናውላለን፡፡ የቅጂ መብት ጉዳይ እንዳታነሡብኝ እንጂ መዝሙራትም እንዲሁ ኾነዋል፡፡
ዛሬ ዘመኑ ፈቀደልንና በድቃቂ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የፈለግነውን ያኽል ፋይሎች ይዘን በፈለግነው ቦታ ጥቅም ላይ እናውላለን፡፡ የቅጂ መብት ጉዳይ እንዳታነሡብኝ እንጂ መዝሙራትም እንዲሁ ኾነዋል፡፡
እንዲህ ከኾነ መዝሙር ስንከፍት ምን ልንጠነቀቅ ይገባል?
፩. ማዳመጥ መቻላችንን ማረጋገጥ
ቅዱስ ዳዊት "ዘምሩ፥ ለአምላካችን ዘምሩ ዘምሩ፥ ለንጉሣችን ዘምሩ። እግዚአብሔር ለምድር ሁሉ ንጉሥ ነውና በማስተዋል ዘምሩ።" ይላል፡፡ መዝ ፵፮፥፮-፯። ከቅዱስ ቃሉ እንደተረዳነው ሲዘመር ማስተዋል ግዴታ ነው፡፡ መንፈስን ሳይሰበስቡ ምስጋና የለም፡፡ ልቡናን ሳያዘጋጁ ምስጋና የለም፡፡ መዝሙር ጸሎት ነው ብለናል፡፡ ስንጸልይ በአንቃዕዶ ልቡና በሰቂለ ኅሊና መኾን ይገባናል፡፡ "ስትጸልዩ … በከንቱ አትደገሙ" ተብለናልና፡፡ ማቴ ፮፥፯።
በሥራ ላይ እያሉ መዝሙር መክፈት የማናዳምጠው ከኾነ ምን ይረባናል? በተሰበሰበ ልቡና ኾነን ማቅረብ የሚገባንን ዝማሬ እንዴት በሜዳ ላይ? ከምንም በላይ ደግሞ እኛ የታላቁ ቅዱስና ሊቅ የቅዱስ ያሬድ ልጆች ይህ ሲጠፋን ማየት ይከብዳል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በደጉ ንጉሥ በአጼ ገብረ መስቀል ፊት ዝማሬውን ሲያቀርብ እርሱም ንጉሡም በተመስጦ ላይ ስለነበሩ በምድር ላይ እየኾነ የነበረውን እስከመርሳት ደርሰው ነበር፡፡ ንገሡ በበትረ መስቀላቸው የቅዱስ ያሬድን እግር እንደወጉት አላወቁም ነበረ፡፡ እርሱም ደግሞ ይበልጡኑ እገሩን በጦር መወጋቱ አልታወቀውም ነበር፡፡
በሥራ ላይ እያሉ መዝሙር መክፈት የማናዳምጠው ከኾነ ምን ይረባናል? በተሰበሰበ ልቡና ኾነን ማቅረብ የሚገባንን ዝማሬ እንዴት በሜዳ ላይ? ከምንም በላይ ደግሞ እኛ የታላቁ ቅዱስና ሊቅ የቅዱስ ያሬድ ልጆች ይህ ሲጠፋን ማየት ይከብዳል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በደጉ ንጉሥ በአጼ ገብረ መስቀል ፊት ዝማሬውን ሲያቀርብ እርሱም ንጉሡም በተመስጦ ላይ ስለነበሩ በምድር ላይ እየኾነ የነበረውን እስከመርሳት ደርሰው ነበር፡፡ ንገሡ በበትረ መስቀላቸው የቅዱስ ያሬድን እግር እንደወጉት አላወቁም ነበረ፡፡ እርሱም ደግሞ ይበልጡኑ እገሩን በጦር መወጋቱ አልታወቀውም ነበር፡፡
ከምን የመጣ ነው? ከተባለ በእግዚአብሔር ፊት በልዩ ተመስጦ ኾነን ልናቀርበው የሚገባን ምስጋና ነውና ከተመስጦ የተነሣ በጦር መወጋትንም ኾነ መወጋት እስከመርሳት ደርሰዋል፡፡ ያለበለዚያ ዘጠኝ እንደጣደችው ሴት እንኾናለን፡፡
አሁን አሁን የምናየው ድርጊት ግን ከዚህ በጣም የራቀ እየኾነ ይገኛል፡፡ አንዳንዶች ክርስቲያን መኾናቸው ይታወቅላቸው ዘንድ፡፡ ሌሎች ደግሞ በእምነት የማይመስሏቸውን "ለመበቀል"፡፡ እኔም መዝሙር አለኝ ዓይነት ፉክክር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ከዘፈን ይሻላል ከማለት፡፡ ዋናው ቁም ነገር ግን እኛ የምንዘምረው ለአገሩ ለመንደሩ ወይ ለጋራ ሸንተረሩ ሳይኾን ለራሳችን መኾኑን አለመዘንጋት ነው፡፡
አሁን አሁን የምናየው ድርጊት ግን ከዚህ በጣም የራቀ እየኾነ ይገኛል፡፡ አንዳንዶች ክርስቲያን መኾናቸው ይታወቅላቸው ዘንድ፡፡ ሌሎች ደግሞ በእምነት የማይመስሏቸውን "ለመበቀል"፡፡ እኔም መዝሙር አለኝ ዓይነት ፉክክር፡፡ አንዳንዶች ደግሞ ከዘፈን ይሻላል ከማለት፡፡ ዋናው ቁም ነገር ግን እኛ የምንዘምረው ለአገሩ ለመንደሩ ወይ ለጋራ ሸንተረሩ ሳይኾን ለራሳችን መኾኑን አለመዘንጋት ነው፡፡
እንዲህ ከተስማማን ደግሞ መቼ እና እንዴት ማድረግ እንዳለብን ልንወሥን ይገባል፡፡ ሌላው ቀርቶ በቤታችንም ስንከፍት እያዳመጥነው መኾናችንን ማረጋገጥ ግዴታ ነው፡፡ ቤቱ የኦርቶዶክስ ነው፣ ወይንም ደግሞ እኛም መዝሙር አለን ዓይነት በቃለ እግዚአብሔር ላይ ጨዋታ አያስፈልግም፡፡
ዛሬ ዛሬ የምናየው ሁኔታ ግን እጅግም ደስ አያሰኝም፡፡ እንዲያው ስንቱን ተችተን እንዘልቀዋለን ከሚል ዝም የሚባሉ ድርጊቶች ወግ፣ ባሕል፣ ሥርዓት እስከመኾን ሲደርሱ ማየቱ ደግሞ የበለጠ ያምማል፡፡ ጥቂት ድግስ ደግሶ የቤቱ ጣሪያ እስኪገለበጥ ድረስ መዝሙር መክፈት ምን ይሉታል? የተጠራው እንዲሰማ ከኾነ በልኩ በመጠኑ ያለበለዚያ በወግ በጨዋታ በሳቅ እና በሁካታ መካካል መዝሙሩ ቢከፈት ለቃለ እግዚአብሔር የሰጠነው ቦታ ምን ላይ ነው?
ዛሬ ዛሬ የምናየው ሁኔታ ግን እጅግም ደስ አያሰኝም፡፡ እንዲያው ስንቱን ተችተን እንዘልቀዋለን ከሚል ዝም የሚባሉ ድርጊቶች ወግ፣ ባሕል፣ ሥርዓት እስከመኾን ሲደርሱ ማየቱ ደግሞ የበለጠ ያምማል፡፡ ጥቂት ድግስ ደግሶ የቤቱ ጣሪያ እስኪገለበጥ ድረስ መዝሙር መክፈት ምን ይሉታል? የተጠራው እንዲሰማ ከኾነ በልኩ በመጠኑ ያለበለዚያ በወግ በጨዋታ በሳቅ እና በሁካታ መካካል መዝሙሩ ቢከፈት ለቃለ እግዚአብሔር የሰጠነው ቦታ ምን ላይ ነው?
፪. በእግዚአብሔር ፊት እንደቆምን ማሰብ
መዝሙር ከመዘመራችን በፊት በዓይነ ኅሊናችን በልዑል እግዚአብሔር እና በቅዱሳኑ ፊት እንደቆምን ልናስብ ይገባል፡፡ ምስጋናው ለእግዚአብሔር እና እርሱ ላከበራቸው ቅዱሳኑ ነውና እንደምናያቸው እያሰብን አኮቴት ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ ማርያም እኅተ አልዓዛር "የማይቀሟትን በጎ ዕድልን መርጣለች" የተባለችው ልቡናዋን ሰብስባ በጌታዋ እግር ሥር ቁጭ ብላ ቃሉን በመስማቷ አይደለምን? ሉቃ ፲፥፵፪። መዝሙርም ይኽን የመንፈስ ዝግጅት ይፈልጋል፡፡
ቅድስት ልድያ ልቡናዋ ተከፍቶላት ቃለ እግዚአብሔርን ሰምታ ክርስትናን ተቀብላ ከነቤተሰብዋ የተጠመቀቸው ፣ ቅዱሳንንም በቤቷ እስከማስተናገድ የደረሰችው በአንቃዕዶ ኅሊና በማዳመጧ ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት የለበሰውን የማዕረግ ልብስ ወልቆበት እንደ ተራ ሰው እስኪመስል ድረስ በታቦተ ጽዮን ፊት የዘመረው ከፊቱ የቆመውን ስላወቀ ነው፡፡ ፪ ሳሙ ፮፥፲፮።
በእኛም ዘንድ ይህ ሊለመድ ይገባል፡፡ በጥቂት በጥቂቱ ራሳችንን እያረምን መስተካከል ከእኛ ከክርስቲያኖች ይጠበቃል፡፡
መዝሙር ከመዘመራችን በፊት በዓይነ ኅሊናችን በልዑል እግዚአብሔር እና በቅዱሳኑ ፊት እንደቆምን ልናስብ ይገባል፡፡ ምስጋናው ለእግዚአብሔር እና እርሱ ላከበራቸው ቅዱሳኑ ነውና እንደምናያቸው እያሰብን አኮቴት ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ ማርያም እኅተ አልዓዛር "የማይቀሟትን በጎ ዕድልን መርጣለች" የተባለችው ልቡናዋን ሰብስባ በጌታዋ እግር ሥር ቁጭ ብላ ቃሉን በመስማቷ አይደለምን? ሉቃ ፲፥፵፪። መዝሙርም ይኽን የመንፈስ ዝግጅት ይፈልጋል፡፡
ቅድስት ልድያ ልቡናዋ ተከፍቶላት ቃለ እግዚአብሔርን ሰምታ ክርስትናን ተቀብላ ከነቤተሰብዋ የተጠመቀቸው ፣ ቅዱሳንንም በቤቷ እስከማስተናገድ የደረሰችው በአንቃዕዶ ኅሊና በማዳመጧ ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት የለበሰውን የማዕረግ ልብስ ወልቆበት እንደ ተራ ሰው እስኪመስል ድረስ በታቦተ ጽዮን ፊት የዘመረው ከፊቱ የቆመውን ስላወቀ ነው፡፡ ፪ ሳሙ ፮፥፲፮።
በእኛም ዘንድ ይህ ሊለመድ ይገባል፡፡ በጥቂት በጥቂቱ ራሳችንን እያረምን መስተካከል ከእኛ ከክርስቲያኖች ይጠበቃል፡፡
፫. ሌሎች ሰዎችን አለመረበሽ
ከዚህ በላይ ያሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ካሟላን ቀጥሎ ሊያሳስበን የሚገባው በዙሪያ ገባችን ያሉት ሰዎች ናቸው፡፡ መቼም የመንዘምረው ሰውን ለማናደድ ፣ ወይም ለማብሸቅ አይደለም፡፡ ለወንድም ለወገን ሲባለ ብዙ የሚተው ነገር ይኖራል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋ መብላቴ ወንድሜን የሚያሰናክል ለኾነ ለዘለዓለሙ ሥጋ አልበላም ያለው ሥጋ መብላት የሚወገዝ ኾኖ አይደለም፡፡ ፩ ቆሮ ፰፥፲፫። ነገር ግን ስለ ሌላው ኅሊና ሲባል ይተዋል፡፡ ክርስትና እንዲህ ነው፡፡ ከራስ አልፎ ለሌሎች የሚኖሩት ሕይወት!
ብዙ የዓለም ነገሮችን የምንጾመው በሕግ በሥርዓት ስለተደነገጉ ብቻ አይደለም፡፡ እንደየደረጃችን ለሰዎች ስንልም ራሳችን በራሳችን ቅር ሳይለን በደስታ የምንተዋቸው ጉዳዮችም አሉ፡፡ ስለዚህ ሁሉ ነገር ተመቻችቶልን ነገር ግን የአካባቢያችን ሁኔታ ያልተመቸ ቢኾን ከእኛ ስንፍና የተነሣ አይሁን እንጂ ብንተው በስውር የሚያይ አምላክ በግልጥ ይከፍለናል፡፡
ደግሞም ጮክ ካለው ይልቅ በለሆሳስ ያለው የበለጠ ውስጥ ድረስ ዘልቆ ይሰማል፡፡ ስለኾነም መዝሙሮቻችን ለእኛ የሚደመጡ ሌላውን የማይረብሹ መኾናቸውን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ እኛ ክርስቲያኖች ከፍ ያለ የመንፈስ ልዕልና ያለን፣ ተቃዋሚዎች እንንቀፍ ቢሉ እንኳ ምክንያት የማይገኝብን ልንኾን ያስፈልጋል፡፡ መጽሐፍ "አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም።" ፪ ቆሮ ፮፥፫። ደግሞም ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ "ስለሚመለከቱት ስለ መልካም ሥራችሁ፥ ክፉ እንደምታደርጉ በዚያ እናንተን በሚያሙበት ነገር፥ በሚጎበኝበት ቀን እግዚአብሔርን ያከብሩት ዘንድ በአሕዛብ መካከል ኑሮአችሁ መልካም ይሁን።" እንዳለው ከሕዝብም ከአሕዛብም ምክንያት ሊገኝብን አይገባም፡፡ ፩ ጴጥ ፪፥፲፪።
ከዚህ በላይ ያሉትን ቅድመ ሁኔታዎች ካሟላን ቀጥሎ ሊያሳስበን የሚገባው በዙሪያ ገባችን ያሉት ሰዎች ናቸው፡፡ መቼም የመንዘምረው ሰውን ለማናደድ ፣ ወይም ለማብሸቅ አይደለም፡፡ ለወንድም ለወገን ሲባለ ብዙ የሚተው ነገር ይኖራል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሥጋ መብላቴ ወንድሜን የሚያሰናክል ለኾነ ለዘለዓለሙ ሥጋ አልበላም ያለው ሥጋ መብላት የሚወገዝ ኾኖ አይደለም፡፡ ፩ ቆሮ ፰፥፲፫። ነገር ግን ስለ ሌላው ኅሊና ሲባል ይተዋል፡፡ ክርስትና እንዲህ ነው፡፡ ከራስ አልፎ ለሌሎች የሚኖሩት ሕይወት!
ብዙ የዓለም ነገሮችን የምንጾመው በሕግ በሥርዓት ስለተደነገጉ ብቻ አይደለም፡፡ እንደየደረጃችን ለሰዎች ስንልም ራሳችን በራሳችን ቅር ሳይለን በደስታ የምንተዋቸው ጉዳዮችም አሉ፡፡ ስለዚህ ሁሉ ነገር ተመቻችቶልን ነገር ግን የአካባቢያችን ሁኔታ ያልተመቸ ቢኾን ከእኛ ስንፍና የተነሣ አይሁን እንጂ ብንተው በስውር የሚያይ አምላክ በግልጥ ይከፍለናል፡፡
ደግሞም ጮክ ካለው ይልቅ በለሆሳስ ያለው የበለጠ ውስጥ ድረስ ዘልቆ ይሰማል፡፡ ስለኾነም መዝሙሮቻችን ለእኛ የሚደመጡ ሌላውን የማይረብሹ መኾናቸውን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ እኛ ክርስቲያኖች ከፍ ያለ የመንፈስ ልዕልና ያለን፣ ተቃዋሚዎች እንንቀፍ ቢሉ እንኳ ምክንያት የማይገኝብን ልንኾን ያስፈልጋል፡፡ መጽሐፍ "አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም።" ፪ ቆሮ ፮፥፫። ደግሞም ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ "ስለሚመለከቱት ስለ መልካም ሥራችሁ፥ ክፉ እንደምታደርጉ በዚያ እናንተን በሚያሙበት ነገር፥ በሚጎበኝበት ቀን እግዚአብሔርን ያከብሩት ዘንድ በአሕዛብ መካከል ኑሮአችሁ መልካም ይሁን።" እንዳለው ከሕዝብም ከአሕዛብም ምክንያት ሊገኝብን አይገባም፡፡ ፩ ጴጥ ፪፥፲፪።
ቀረኝ
በእጅ ስልኮቻችን ማለትም በተንቀሳቃሽ ስልኮች የጥሪ ድምጽ ያደረግናቸው መዝሙሮችስ አያሳዝኗችሁምን? አንዳንዶች ገና የእግዚአብሔርን ስም ጠርተው ሳይጨርሱ " እግ" እንዳሉ ጉሮሯቸውን ይታነቃሉ፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ሲጠሩ ይውላሉ እንጂ ምን እንደሚሉ የሚሰማቸው የለም፡፡ የደወለውን ሰው ማነጋገር ያልፈለጉ እንደኾን ደግሞ ድምጻቸው ይዘጋል፡፡ እንዲያው ምኑ ቅጡ፡፡ ግን ይኽ ሁሉ የሚኾነው ለእግዚአብሔር በሚቀርበው መዝሙር ላይ ነውን? ጎበዝ በጊዜ ወደ ልቡናችን እንመለስ፡፡ ጨርሶ ለተንቀሳቃሽ የስልክ መጥሪያ መዝሙራትን መጠቀም ከዓላማው ጋር አብሮ አይሄድምና እባካችሁ ስልኮቻችሁን አስተካክሉ፡፡
No comments:
Post a Comment