☞አንብበው ካልጨረሱት አይጀምሩት!!! ከጨረሱት ለጓደኛወ ያካፍሉት!!
ስለ አዳምና ሄዋን ጥያቄ ከነ መልሱ
1/ እግዚአብሔር አዳምን ከፍጥረታት መጨረሻ ለምን ፈጠረው?
2/ እግዚአብሔር ሌሎችን ፍጥረታት አስጎንብሶ ሲፈጥራቸው አዳምን አቅንቶ ለምን ፈጠረው?
3/ እግዚአብሔር አዳምን ለሚቆም ፣የሚተኛ አድርጎ ለምን ፈጠረው?
4/ እግዚአብሔር ለአዳም ስንት ሀብታትን ሰጠው? ምንምን ናቸው?
5/ እግዚአብሔር ሄዋንን ከአዳም ከጎኑ አጥንት ለምን ፈጠራት ? ከግንባር ወይም ከ እግር ለምን አልፈጠራትም?
6/ በገነት ውስጥ ስንት አይነት ዛፎች ነበሩ?
7/አዳምና ሄዋን የእግዚአብሔርን ህግ በማክበር በገነት ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ቆዩ?
8/ አዳምና ሄዋንን በእባቢቱ ላይ አድሮ ያሳታቸው ሰይጣን ስም ማን ይባላል?
9/አዳምና ሄዋን ስንት ልጆች ነበራቸው ?
10/ አዳም በተፈጠረ በስንት አመቱ አረፈ?
አዳም ማለት ከመሬት የተፈጠረ ያማረ መልከ መልካም ማለት ሲሆን የተፈጠረው ከአራት ባህርያተ ስጋ ማለትም ከነፋስ፣ከእሳት ፣ከውሀ፣ከመሬት እንድሁም ከሶስቱ ባህርያተ ነፍስ ማለትም ከልብ ፣ከቃል፣ከእስትፋስ
የስነ ፍጥረት መካተቻ በሆነች በእለተ አርብ በ3 ስዓተከህቱም ምድር ሚያዝያ 4 ቀን በምድር መካከል በምትገኘው <ኤልዳ> በተባለች ስፍራ የ30 አመት ጎልማሳ ሁኖ በእግዚአብሔር አርአያነት መልክ ተፈጠረ፡፡
ኦሪት ዘፍጥረት 1፣27 ፣ኩፉሌ 5፣6
መልስ ፡-
1/አዳም ከፍጥረታት መጨረሻ ለምን ተፈጠረ?
☞መጨረሻ የተፈጠረበት ምክንያት እግዚአብሔር አምላካችን "በጎ አምላክ" ስለሆነ በጎ አባት ለልጁ አብሮት ከብት ያረባለታል ፣ጥማጅ ያጠምድለታል፣ የኑሮ ጓደኛ ያመጣለታል አስቀድሞየሚበላው፣የሚጠጣው፣የሚገዛውና የሚነዳውን ፈጥሮለት በመጨረሻም በሁሉ ላይ ሊያሰለጥነው አዳምን ፈጠረው፡፡
2/ ሌሎችን ፍጥረታት አስጎንብሶ ሲፈጥራቸው አዳምን ለምን አቅንቶ ፈጠረው?
☞ እሱ ገዥ እናተ ተገዥ ናችሁ ሲል ነወ፣እንድሁም እናተ ፈርሳችሁ በሰብሳላችሁ ትቀራላችሁ እሱ ግን" ትንሳኤ ሙታን " አለው ሲል አቅንቶ ፈጠረው፡፡
3/ አዳምን የሚቆም የሚተኛ አድርጎ ለምን ፈጠረው?
☞ መቆሙ- ሰማያዊ ፣
☞መቀመጡ- ምድራዊ ነህ ሲለው ነው፣
☞የሚተኛ ፣ የሚነሳ አድርጎ መፍጠሩ ደግሞ ☞መተኛቱ- ሞቱን
☞መነሳቱ - ትንሳኤውን ሲነግረው ነው፡፡
4/ እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም ስንት ሀብታት ሰጠው? ምን ምን?
☞ሰባት ሀብታትን የሰጠው ሲሆን እነሱም፡-
➊ሀብተ መንግስት (የማስተዳደር ሀብት
➋ሀብተ ክህነት ( የመቀደስ፣የመባረክ፣መስዋዕት የማቅረብ
➌ ሀብተ ትንቢት (የመጣውን የመናገር
➍ሀብተ መዋኢ (የማሸነፍ
➎ሀብተ ሀይል (የጥንካሬ
➏ሀብተ ፈውስ ( የመዳን ፣የመፈወስ
➐ሀብተ ዝምሬ (የመዝሙር
5/ ሄዋን ከአዳም ከጎኑ አጥንት ወስዶ ለምን ተሰራች?ከግንባር ወይም ከእግር ለምን አልሰራትም?
☞ አዳም ለእንሰሳት፣ለሰማይ ወፎች ና ለምድር አራዊቶች ሁሉ ተባእትና እንስት ሁነው ሲመጡ ስም ያወጣላቸው ነበር፡፡ነገር ግን ለአዳም እንደ ራሱ ያለ ረዳት አልተገኘለትም ነበር ፡፡
"እግዚአብሔርም " ሰው ብቻውን ይሆን ዘንድ መልካም አይደለም የሚመቸውን ረዳት ልፍጥርለት አለ ፡፡ኦዘፍ 2፣18
ከዚያም በአዳም ላይ እንቅልፍ አመጣበትና ፈፅሞ ሳይተኛ ፣ፈፅሞ ሳይነቃ ከጎኑ አጥንት አንስት አንስቶ ያችን ስጋ አልብሶ የ15 አመት ቆንጆ አድርጎ ፈጠራት ፣ኦዘፍ 2፣18
አዳምም ስሟንም "ሄዋን" አላት ፣ሄዋን ማለት "ሀይው" ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም" የህያዋን ሁሉ እናት "ማለት ነው፡፡
ፈፅሞ ሳይተኛ ፣ፈፅሞ ሳይነቃ ሄዋንን መፍጠሩ
☞ፈፅሞ ተኝቶ ቢሆን ኑሮ ምትሀት መስሎት ከየት መጣች ብሎ ይፈራታል
☞ፈፅሞ ነቅቶ ቢሆን ኑሮ ከአካሉ አጥንት ሲነሳለት ያመው ነበርና ይጠላት ነበር ፡፡
☞ከፍ አድርጎ ከግባር ዝቅ አድርጎ ከእግር ያልሰራት ግባርና እግር በልብስ አይሸፈንም ጎኑ ግን በልብስ ይሸፈናልና ተሰውራ ወይም ተሸፍና መኖር ይገባታል ሲል ነው፡፡
በሌላ በኩል ግንባር የባለቤት እግር፣ የቤተሰብ ምሳሌ ነው ፡እሷም ከባለቤቷ በስተታች ከቤተሰብ በላይ ሁና ትኑር ሲል ነው ፡፡ 1ኛ ቆሮ 12፣19-22
እንድህ አድርጎ አዳምና ሄዋንን እስከ 40 ቀን ድረስ በተፈጠሩበት በማዕለ ምድር በቀራንዮ አስናበታቸው
ጌታችን አምላካችንና መድሀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የሚሰቀልበት ቦታ ነውና ከዛም በ40ኛው ቀን አዳምን ብርሃን አልብሰው ፣ብርሀን አጎናፅፈው፣የብርሀን ዘውድ አቀናጅተው በብርሃን ሰረገላ አስቀምጠው ወደ ገነት አስገቡት፡፡
ሄዋንንም በ80 ቀኗ እንደ አዳም ባለ ክብር ወደ ገነት አስገቧት ፡፡ኩፉሌ ፈ 4፣12-15
አዳምና ሄዋን ከእግዚአብሔር የባህሪ ደግነት የተነሳ እርሱን ለማመስገንና ክብሩን ለመውረስ ተፈጠሩ፡፡ ኩፋሌ 4 ፣3-5
እግዚአብሔር ለአዳም ረዳት የፈጠረለት ስለ ሶስት ነገሮች ሲል ነው፡፡
➊ዘርን ለማብዛት
➋ ከዝሙት እንድፀዳና
➌ረዳት እንድትሆነው ነው
6/ በገነት ውስጥ 3 አይነት ዛፎች ነበሩ
➊ ዕፀ መብል -እንድበሉት የተፈቀደላቸው ምግብ ነው
➋ዕፀ በለስ-እንዳይበሉ የታዘዙት ነው
➌ዕፀ ህይወት - እንደ <እግዚአብሔር > ፈቃድ የሚመገቡት የዘለዓለም ህይወት የሚሰጥ ምግብ ነው፡፡
ህግን ጠብቀው በገነት ውስጥ 1000 አመት ከኖሩ ብኀላ እፀ ህይወት በልተው ከገነት ወደ ሰማያዊ እየሩሳሌም (መንግስተ ሰማይ ) እንድገቡ ለበለጠ ክብርና ፀጋ ሽልማት እንድሎናቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ያለ ጊዜው ሳቱ እንጅ
'እፀ በለስ ' እንዳይበሉ የታዘዙበት ህግ አዳም ፈጣሪ እንዳለው ፣ለፈጣሪው ያለውን ፍቅር የሚገልፅበትና ተገዥነቱን የሚያሳይበት ነው፡፡
7/ አዳምና ሄዋን የእግዚአብሔርን ህግ በማክበር በገነት ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ቆዩ?
☞አዳምና ሄዋን ይህን ህግ በማክበር በገነት ውስጥ ለ7 አመት ከ 2ወር ከ 17 ቀን ኖሩ፡፡
8/ አዳምና ሄዋንን በእባብ ላይ አድሮ ያሳታቸው ሰይጣን ስም ማን ይባላል ?
☞አዳም በሳጥናኤል ተተክቶ መቶኛ ሁኖ ከመላእክት ጋር ተቆጥሮ ነበር ሰይጣንም በእባብ አድሮ አሳቻቸው ጽድቃቸውም ተገፈፈ አዳምና ሄዋንን በእባብ ላይ አድሮ ያሳታቸው ሰይጣን ስም ' ጋርድኤል ይባላል፡፡
በመሆኑም አትብሉ የተባሉትን እፀ በለስ ህጉን አፈረሱ ከገነት ተባረሩ ፡ኦዘፍ 3፣1 ኦዘፍ 3 ፣22-24
9/ አዳምና ሄዋን ስንት ልጆች ነበሯቸው?
☞ ከገነት ከተባረሩ ብኀላ በደብረ ቅድስት ይኖሩ ነበር፡
አዳምና ሄዋን በሰሩት ሀጢያት በመፀፀታቸውና በንሰሀ በመመለሳቸው "እግዚአብሔር" መሀሪ ነውና 5 ቀን ተኩል ወይም 5500 ዘመን ሲፈፀም ሰው ሁኖ በመወለድ እንደሚያድናቸው ቃል ኪዳን ገባላቻው ፡፡ኦዘፍ 3፣15-22
አዳም ግን የራሱን ደም በስንደ ለውሶ ሲሰዋ ጌታችን በአንተ ደም አይደለም አለም የሚድነው በእኔ ነው ብሎ ተስፋ ሰጠው፡፡
አዳምና ሄዋንም በምድር ላይ ዘርን ተክተዋል ገብርኤል ፣ሚካኤል ፣ሩፋኤል ወርቅ ,እጣን,ከርቤ አምጥተው ለአዳም ሲሰጡት ወርቁን ማጫ ይሁንሽ ብሎ ሰጣት ከዛም አዳምና ሄዋን በ 30 ሩካቤ 60 ልጆችን ወልደዋል
10/ አዳም በተፈጠረ በስንት አመቱ አረፈ?
☞ አዳም በተፈጠረ በ930 አመቱ አረፋ ፡አዳም ለሄዋን የሰጣት ወርቅ ለሴት ሰጠችው ሴትም ለኖህ አስተላለፈው እጣኑንም ኖህ አፅመ አዳም እያጠነ ድኖበታል ፡፡
በአዳም ስም በሀገራችን የተሰሩ ቤተክርስቲያኖች ብዛታቸው 5 ናቸው
በአዳም ስም የተቀረፀው ታቦት ከሶሪያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ያመጣው ፃድቅ አባት 'መልከአ እግዚአብሔር ' ይባላል፡፡እንድከበር ያደረገው ቅዱስና ሊቁ ያሬድ ማህሌት ነው፡፡
----------ምንጭ----------
መፅሀፈ ኩፉሌ
ኦሪት ዘፍጥረት
ዜና አዳም
ገድለ አዳም
ዜና አበው
ቅዱሳን ታሪክ
---------------------------------
ለአባ ህርያቆብ ፣ለቅዱስ ኤፍሬም ፣ለቅዱስ ያሬድ፣ለአባ ጊወርጊስ ዘጋስጫ የተገለፀች እመቤታችን እኛንም በበረከትና በረድኤት ተጎብኘን ከልጇ ከወዳጇ ከመድሀኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ታማልደን አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላድቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክብር
አሜን
Image may contain: 2 people , text