Thursday, 26 May 2016

እመቤታችን የት ተወለደች?

እመቤታችን ስለተወለደችበት ስፍራ በዓለም የተለያዩ ሀሳቦች ሲሰነዘሩ ቆይተዋል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ሀሳቦች የሚያነሡ ሲሆን አንደኛው “ድንግል ማርያም ብስራተ መልአክ በሰማችበት ናዝሬት ተወልዳለች” የሚል ነው፡፡ ሁለተኛው ሀሳብ ደግሞ “ከሦስተኛው ክ/ዘመን ወዲህ የማርያም መግቢያ ተብሎ በሚታወቀው ከኢየሩሳሌም የቅድስት ሀና የክሩሲድ ቤተ ክርስቲያን በታች ነው የተወለደችው” የሚል መላ ምታዊ አመለካከት ነው፡
የኮፕቲክ (ግብጽ) ስንክሳር “የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ በናዝሬት ነው” ይላል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስንክሳር ግን በቀደምትነታቸው ተጠብቀው የቆዩ ከመሆናቸው አንጻር ተአማኒነታቸው የጎላ መሆኑን ያሳያል፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡ ሊባኖስ ከገሊላ በስተ ሰሜንና ከፍንቄ በስተ ምስራቅ ይገኛል፡፡ “ሙሽራየ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ” የሚለው ቃለ ትንቢት ምስጢርም የአመቤታችን መካነ ልደት የሊባኖስ ተራራ ስለመሆኑ የሚያጠይቅ እንደሆነ ምስክርነታቸው የታመነ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ /መኃ 4፥7/፡፡
121
የእመቤታችን የትውልድ ሀረግ
በእግዚአብሔር ፊት የተወደዱ በምግባር በሃይማኖት ጸንተው ይኖሩ የነበሩ የእመቤታችን ቅድመ አያቶች ቴክታና በጥሪቃ ይባላሉ፡፡ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጸጎች ነበሩ፡፡ የሃብታቸው ብዛት ሥፍር ቁጥር አልነበረውም፡፡
ከዕለታት ባንደኛው ቀን ቴክታ ወደ ቤተ መዛግብቱ ገብቶ የገንዘቡን ብዛት ሲያይ እኔ መካን አንቺም መካን ይህ ሁሉ ገንዘብ ለማን ይሆናል?” አላት፡፡ እግዚአብሔር ከእኔ ልጅ ባይሰጥህ ሌላ አግብተህ ትወልድ ዘንድ ፈቅጄልሃለሁ አለችው፡፡ ይህን እንዳላደርገው አምላከ እስራኤል ያውቃል አላት፡፡ በዚህ እያዘኑ ሳለ ወዲያው ራእይ ታያቸው፡፡ ይህም ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወረደች እስከ ስድስት ስትደርስ ስድስተኛይቱ ጨረቃን፣ ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሀገራቸው ወደ ነበረው ሕልም ፈቺ ሔደው ነገሩት፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ የተቃኘው ሕልም ፈቺም ‹‹ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡ ጨረቃይቱ ከፍጡራን በላይ የምትሆን ልጅ ነች፡፡ የፀሐዩ ነገር ግን አልተገለጸልኝም›› አላቸው፡፡ እነሱም ይህንን ጊዜ ይፍታው ብለው ወደ ቤታቸው ሔዱ፡፡ ከዚህ በኋላ በጥሪቃ ፀነሰች፤ ወለደችም፤ ሄኤሜን አለቻት፡፡ ሄኤሜን ዴርዴን፣ ዴርዴ ቶናን፣ ቶና ሲካርን፣ ሲካር ሄርሜላን፣ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡
ሐና ማለት በሃይማኖት በምግባር የጸናች፤ በንጽሕና በቅድስና የተሸለመች ቡርክት ክብርት ደግ ፍጥረት ማለት ነው፡፡ ይህችን በምግባር በሃይማኖት ተኮትኩታ ያደገች ሴት አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ ይሁዳ ለተወለደው ኢያቄብ ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት፡፡ ሐናና ኢያቄብ በፍቅርና በደስታ ኑሮአቸውን ቢመሩም በአያታቸው የደረሰው መካንነት በእነሱም ላይ ደረሰ፡፡ በተሰበረ ልብ እግዚአብሔር የሐናን ማሕፀን ይከፍት ዘንድ በጸሎት ይማጸኑት ጀመር፡፡ የሐና ጎረቤት የሆነች በዝሙት ሥራ የምትኖር አንዲት ሴት ነበረች፡፡ ሐናም ቀረብ ብላ “ዛሬ ቤተ እግዚአብሔር ስስማለሁ ብዬ ነበር፤ ነገር ግን የምለብሰው ልብስ የለኝም” አለቻት፡፡ ይቺም ሴት መልሳ “ካንድም ሁለት ሦስት የእኔ ልብስ አለልሽ፤ ያን ለብሰሽ ለምን አትሔጅም?” ብትላት ሐና ግን በኃጢአት ሥራ የተገኘ ልብስ ነው፡፡ እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ ስለሆነ ይህ አይሆንልኝምብላ መለሰችላት፡፡ ይህቺ ሴት ከኃጢአት ሥራዋ ታርማ የጽድቅ ሥራ ለመሥራት ለማሰብ ይልቅ ልብ የሚነካ ነገር ተናገረቻት፤ “በምን ምክንያት ልጅ ነሳሽ ብዬ ሳዝን ነበር፤ ለካ እንደ ድንጋይ አድርቆ ያስቀረሽ ይህ ክፋትሽ ነው!” በዚህ ንግግሯ ሐና እጅግ አዘነች፡፡
images
በሌላ ጊዜም ከቧላ ከኢያቄም ጋር ቤተ መቅደስ ሔደው መስዋዕት ለማቅረብ ሲሔዱ ሊቀ ካህናቱ ሮቤል የመካኖች መስዋዕት አትቅበል ይላል፤ እናንተ ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት ያለውን የአዳምን ቃል ያስቀረባችሁ አይደላችሁንም? እግዚአብሔር ቢጠላችሁ እንጂ ቢወዳችሁማ ልጅ በሰጣችሁ፤ መስዋዕቱንም ለማቅረብ እድል ባገኛችሁ ብሎ መለሳቸው፡፡ በዚህ አዝነው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሳለ ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲጨዋወቱ ዕፀዋት አብበው አፍርተው አዩ፡፡ በዚህን ጊዜ እንዲህ ብለው ጸለዩ ርግቦችን እንዲራቡ ዕፀዋትም እንዲያብቡና እንዲያፈሩ የምታደርግ የእኛ ተፈጥሮ ከድንጋይ ስለሆነ ነው ልጅ የነሳኸን?”ብለው አዘኑ፡፡ ከዚህ በኋላ ሐናና ኢያቄም የለመኑትን ለማይነሳ የነገሩትን ለማይረሳ አምላክ ብትአታቸውን (ሥለታቸውን) አስነቡና ‹‹ወንድ ልጅ ብንወልድ ወጥቶ ወርዶ አርሶ ቆፍሮ ይርዳን አንልም ለቤተ እግዚአብሔር አንጣፊ ጋራጅ ይሆናል፡፡ ሴት ብንወልድ እንጨት ሰብራ ውኃ ቀድታ ትርዳን አንልም ለቤተ እግዚአብሔር መሶበ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ትኑር›› በማለት ለመኑ፡፡ ሐምሌ 30 ቀን ድንቅ ሕልም ተመለከቱ ከአንድ ሱባኤ በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ በማለት አበሠራቸው፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔር በቅዱስ ገብርኤል አብሣሪነት እመቤታችን ነሐሴ ሰባት ቀን ተፀነሰች
አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ከዚህ ቀደም ከነሱ ወገን የሚሆኑ ዳዊትና ሰሎሞን አርባ አርባ ዘመን እንሰም አቅልጠው እንደገል ቀጥቅጠው ገዙን፤ ከእነሱ ደግሞ የሚወለደውን እንደምን ያደርገን ይሆን? ብለው በጠላትነት ተነሱባቸው፡፡ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ትእዛዝና መሪነት ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ወደ ሊባኖስ ተራራ ወጡ፡፡ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ መሠረቶቹ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው ብሎ እንደተናገረው ከተቀደሱ ወላጆቿ ግንቦት 1 ቀን በተራራው ላይ ሳሉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች /መዝ. 86፥1/፡፡
ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ጸሎቱ ጸጋን የተመላሽና የደስታ መገኛ ሆይ ዓይኖቻቸው ብዙዎች ከሚሆኑ ከኪሩቤልና ክንፎቻቸው ስድስት ከሆኑ ከሱራፌል ግርማ የሚበልጥ የመወደድ ግርማ አለሽ፡፡ እነዚያ ፊታቸውን ይሸፍናሉከልጅሽ መለኮት ከሚወጣው እሳት ይድኑ ዘንድ፤ አንቺ ግን የመለኮት ማደሪያ ሆንሽ፤ የመለኮት ባሕርይም ሥጋሽን አላቃጠለውም፤ የእሳት ነበልባልን ተሸከምሽ ብሏታል፡
በቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት መሠረት ሃና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደው በአድባረ ሊባኖስ ሥር  እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸው “ንፍሮና ጥራጥሬ” ነበር፡፡ይኼንን ትውፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ውጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማውን ማስፈጸም የሚፈልገው ዲያብሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸው መንፈሳዊያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነው፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለውጋር ነው፣ቆሌውን ለመለመን ነው፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ቡና የሚረጩ፣ቂቤ የሚቀቡ፣የከብት ደም የሚያፈሱ፣  እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡
ሃይማኖታዊ ሥርዐት እያደገ ጠቃሚ ባህል ወደ መሆን ለመወጡ ደስ ያሰኛል፡፡ ወገኖቻችንም በእመቤታችን የልደት ቀን የተቸገረውን በመርዳት በዓሏን ለማክበር ሚያደርጉት ጥረት መልካም በመሆኑ ሊበረታታ ይገባዋል፡፡ በልደታ ማርያም በዓል ሰበብ የሚደረግ ጣዖት የማምለክ ሥርዐት ካለ ደግሞ የቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት አይደለምና እናውግዘው፡፡ ስለሆነም ይኼንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር እንድናከብረው የእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን፡፡ አሜን!!
በእግዚአብሔር ፊት የተወደዱ በምግባር በሃይማኖት ጸንተው ይኖሩ የነበሩ የእመቤታችን ቅድመ አያቶች ቴክታና በጥሪቃ ይባላሉ፡፡ ይህ ቀራቸው የማይባሉ ባለጸጎች ነበሩ፡፡ የሃብታቸው ብዛት ሥፍር ቁጥር አልነበረውም፡፡
ከዕለታት ባንደኛው ቀን ቴክታ ወደ ቤተ መዛግብቱ ገብቶ የገንዘቡን ብዛት ሲያይ እኔ መካን አንቺም መካን ይህ ሁሉ ገንዘብ ለማን ይሆናል?” አላት፡፡ እግዚአብሔር ከእኔ ልጅ ባይሰጥህ ሌላ አግብተህ ትወልድ ዘንድ ፈቅጄልሃለሁ አለችው፡፡ ይህን እንዳላደርገው አምላከ እስራኤል ያውቃል አላት፡፡ በዚህ እያዘኑ ሳለ ወዲያው ራእይ ታያቸው፡፡ ይህም ነጭ እንቦሳ ከበረታቸው ስትወጣ እንቦሳይቱ እንቦሳ እየወረደች እስከ ስድስት ስትደርስ ስድስተኛይቱ ጨረቃን፣ ጨረቃ ፀሐይን ስትወልድ አይተው በሀገራቸው ወደ ነበረው ሕልም ፈቺ ሔደው ነገሩት፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ የተቃኘው ሕልም ፈቺም ‹‹ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡ ጨረቃይቱ ከፍጡራን በላይ የምትሆን ልጅ ነች፡፡ የፀሐዩ ነገር ግን አልተገለጸልኝም›› አላቸው፡፡ እነሱም ይህንን ጊዜ ይፍታው ብለው ወደ ቤታቸው ሔዱ፡፡ ከዚህ በኋላ በጥሪቃ ፀነሰች፤ ወለደችም፤ ሄኤሜን አለቻት፡፡ ሄኤሜን ዴርዴን፣ ዴርዴ ቶናን፣ ቶና ሲካርን፣ ሲካር ሄርሜላን፣ ሄርሜላ ሐናን ወለደች፡፡
ሐና ማለት በሃይማኖት በምግባር የጸናች፤ በንጽሕና በቅድስና የተሸለመች ቡርክት ክብርት ደግ ፍጥረት ማለት ነው፡፡ ይህችን በምግባር በሃይማኖት ተኮትኩታ ያደገች ሴት አካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ ይሁዳ ለተወለደው ኢያቄብ ለሚባል ደግ ሰው አጋቧት፡፡ ሐናና ኢያቄብ በፍቅርና በደስታ ኑሮአቸውን ቢመሩም በአያታቸው የደረሰው መካንነት በእነሱም ላይ ደረሰ፡፡ በተሰበረ ልብ እግዚአብሔር የሐናን ማሕፀን ይከፍት ዘንድ በጸሎት ይማጸኑት ጀመር፡፡ የሐና ጎረቤት የሆነች በዝሙት ሥራ የምትኖር አንዲት ሴት ነበረች፡፡ ሐናም ቀረብ ብላ “ዛሬ ቤተ እግዚአብሔር ስስማለሁ ብዬ ነበር፤ ነገር ግን የምለብሰው ልብስ የለኝም” አለቻት፡፡ ይቺም ሴት መልሳ “ካንድም ሁለት ሦስት የእኔ ልብስ አለልሽ፤ ያን ለብሰሽ ለምን አትሔጅም?” ብትላት ሐና ግን በኃጢአት ሥራ የተገኘ ልብስ ነው፡፡ እግዚአብሔር ንጹሐ ባሕርይ ስለሆነ ይህ አይሆንልኝምብላ መለሰችላት፡፡ ይህቺ ሴት ከኃጢአት ሥራዋ ታርማ የጽድቅ ሥራ ለመሥራት ለማሰብ ይልቅ ልብ የሚነካ ነገር ተናገረቻት፤ “በምን ምክንያት ልጅ ነሳሽ ብዬ ሳዝን ነበር፤ ለካ እንደ ድንጋይ አድርቆ ያስቀረሽ ይህ ክፋትሽ ነው!” በዚህ ንግግሯ ሐና እጅግ አዘነች፡፡
በሌላ ጊዜም ከቧላ ከኢያቄም ጋር ቤተ መቅደስ ሔደው መስዋዕት ለማቅረብ ሲሔዱ ሊቀ ካህናቱ ሮቤል የመካኖች መስዋዕት አትቅበል ይላል፤ እናንተ ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት ያለውን የአዳምን ቃል ያስቀረባችሁ አይደላችሁንም? እግዚአብሔር ቢጠላችሁ እንጂ ቢወዳችሁማ ልጅ በሰጣችሁ፤ መስዋዕቱንም ለማቅረብ እድል ባገኛችሁ ብሎ መለሳቸው፡፡ በዚህ አዝነው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሳለ ርግቦች ከልጆቻቸው ጋር ሲጨዋወቱ ዕፀዋት አብበው አፍርተው አዩ፡፡ በዚህን ጊዜ እንዲህ ብለው ጸለዩ ርግቦችን እንዲራቡ ዕፀዋትም እንዲያብቡና እንዲያፈሩ የምታደርግ የእኛ ተፈጥሮ ከድንጋይ ስለሆነ ነው ልጅ የነሳኸን?”ብለው አዘኑ፡፡ ከዚህ በኋላ ሐናና ኢያቄም የለመኑትን ለማይነሳ የነገሩትን ለማይረሳ አምላክ ብትአታቸውን (ሥለታቸውን) አስነቡና ‹‹ወንድ ልጅ ብንወልድ ወጥቶ ወርዶ አርሶ ቆፍሮ ይርዳን አንልም ለቤተ እግዚአብሔር አንጣፊ ጋራጅ ይሆናል፡፡ ሴት ብንወልድ እንጨት ሰብራ ውኃ ቀድታ ትርዳን አንልም ለቤተ እግዚአብሔር መሶበ ወርቅ ሰፍታ መጋረጃ ፈትላ ትኑር›› በማለት ለመኑ፡፡ ሐምሌ 30 ቀን ድንቅ ሕልም ተመለከቱ ከአንድ ሱባኤ በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ በማለት አበሠራቸው፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔር በቅዱስ ገብርኤል አብሣሪነት እመቤታችን ነሐሴ ሰባት ቀን ተፀነሰች
አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ከዚህ ቀደም ከነሱ ወገን የሚሆኑ ዳዊትና ሰሎሞን አርባ አርባ ዘመን እንሰም አቅልጠው እንደገል ቀጥቅጠው ገዙን፤ ከእነሱ ደግሞ የሚወለደውን እንደምን ያደርገን ይሆን? ብለው በጠላትነት ተነሱባቸው፡፡ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ትእዛዝና መሪነት ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ወደ ሊባኖስ ተራራ ወጡ፡፡ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ መሠረቶቹ በተቀደሱ ተራሮች ናቸው ብሎ እንደተናገረው ከተቀደሱ ወላጆቿ ግንቦት 1 ቀን በተራራው ላይ ሳሉ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች /መዝ. 86፥1/፡፡
ቅዱስ ያሬድ በአንቀጸ ብርሃን ጸሎቱ ጸጋን የተመላሽና የደስታ መገኛ ሆይ ዓይኖቻቸው ብዙዎች ከሚሆኑ ከኪሩቤልና ክንፎቻቸው ስድስት ከሆኑ ከሱራፌል ግርማ የሚበልጥ የመወደድ ግርማ አለሽ፡፡ እነዚያ ፊታቸውን ይሸፍናሉከልጅሽ መለኮት ከሚወጣው እሳት ይድኑ ዘንድ፤ አንቺ ግን የመለኮት ማደሪያ ሆንሽ፤ የመለኮት ባሕርይም ሥጋሽን አላቃጠለውም፤ የእሳት ነበልባልን ተሸከምሽ ብሏታል፡
በቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት መሠረት ሃና እና ኢያቄም ከአይሁድ ለማምለጥ ተሰደው በአድባረ ሊባኖስ ሥር  እመቤታችንን ወለዱ በወቅቱ ከቤት የወጡት ለሽሽት ነበርና ስንቅ ስላልያዙ ምግባቸው “ንፍሮና ጥራጥሬ” ነበር፡፡ይኼንን ትውፊት በመያዝ በዓሉ ከቤት ውጭ ንፍሮ እየተበላ ይከበራል፡፡ ሆኖም በበጎ ነገሮች ሰበብ ክፉ ዓላማውን ማስፈጸም የሚፈልገው ዲያብሎስ በማር መሃል መርዝን ከሚጨምርባቸው መንፈሳዊያት በዓላት አንዱ የግንቦት ልደታ የእመቤታችን በዓል ነው፡፡ አንዳንዶች በድፍረት ለአድባር ለውጋር ነው፣ቆሌውን ለመለመን ነው፣ እያሉ ንፍሮ የሚበትኑ፣ቡና የሚረጩ፣ቂቤ የሚቀቡ፣የከብት ደም የሚያፈሱ፣  እነዚህ በእርግጥም ጣዖት አምላኪዎች ናቸው፡፡
ሃይማኖታዊ ሥርዐት እያደገ ጠቃሚ ባህል ወደ መሆን ለመወጡ ደስ ያሰኛል፡፡ ወገኖቻችንም በእመቤታችን የልደት ቀን የተቸገረውን በመርዳት በዓሏን ለማክበር ሚያደርጉት ጥረት መልካም በመሆኑ ሊበረታታ ይገባዋል፡፡ በልደታ ማርያም በዓል ሰበብ የሚደረግ ጣዖት የማምለክ ሥርዐት ካለ ደግሞ የቤተ ክርስቲያናችን ትውፊት አይደለምና እናውግዘው፡፡ ስለሆነም ይኼንን ታላቅ በዓል በተገባና በተረዳ ነገር እንድናከብረው የእመቤታችን ረድኤት በረከት አይለየን፡፡ አሜን!!

ሚካኤል

 
St.Michael1
ሚካኤል ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ ሚ-መኑ’ ካ-ከመ’ ኤል- አምላክ ማለት ሲሆን በአንድነት ሲነበብ መኑ ከመ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው) ማለት ነው፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራዕዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ›› ብሎ ከተናገረላቸው መላእክት ውስጥ የሚመደብ ሲሆን የሰባቱም ሊቃነ መላእክት አለቃ እንዲሆን እግዚአብሔር መርጦ ሹሞታል፡፡ ይህ ታላቅ መልአክ ያደረጋቸው የሠራቸው እጅግ ብዙ የሆኑ ተአምራት አሉት፡፡
ስለዚህ ስለ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ክብር፤ ጠባቂነትና አማላጅነት ከአባቶቻቸው የተማሩትን በኑሮአቸው ያዩትን አባቶቻችን ጽፈዋል፡፡ ስለ ቅዱስ ሚካኤል ከጻፉት አባቶች መካከል የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል፡-
  • ዮሐንስ አፈወርቅ
    + ኤዎስጣቴዎስ ዘአንፆኪያ
    + ቅዱስ መቃርዮስ
    + ቅዱስ ያሬድ
    + አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
    + የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አባዲማቴዎስ ናቸው፡፡
እኛም የአባቶቻችንን አንደበት አንደበታችን አድርገን በኅዳር 12 ክቡር ገናና የሆነ ቅዱስ ሚካኤል ካደረጋቸውና ከሠራቸው ብዙ ተአምራት ውስጥ የተወሰኑትን በመልአኩ ተረዳኢነት እንዲህ ብለን እንናገራለን አንጽፋለን፡፡
      ንግሥት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ጣዖት የሠራችው ቤተ ጣዖት በእስክንድርያ ነበር፡፡ ይህ ቤተ ጣዖት እስከ እስክንድርያው ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312 – 326/ ዘመን ድረስ ነበር፡፡ እለ እስክንድሮስ ሊያጠፋው ሲነሣ ሕዝቡ ከልቡ ገና የአምልኮ ጣዖት ስላልጣፋ 18 ፓትርያርኮች ያልነኩትን አንተ ለምን ታፈርስብናለህ ብለው ተቃወሙት፡፡ እለ እስክንድሮስም ሕዝቡን መክሮና አስተምሮ የሳተርን በዓል ይውልበት በነበረው ዕለት የቅዱስ ሚካኤልን በዓል እንዲያከብሩ አውጆ ቤተ ጣዖቱንም በቅዱስ ሚካኤል ስም ሰይሞ ቤተክርስቲያን አደረገው፡፡ ከዚህ በኋላ በቅዱስ ሚካኤልም ስም አብያተ ክርስቲያናት መታነጽ ጀመሩ  በዓሉ በዚህ ቀን እንዲከበር ተወስኗል፡፡
     እንዲህም ሆነ የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ ስሙ ዱራታዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፡፡ የሚስቱም ስም ቴዋብለት ነው፡፡ እነርሱም ሁልጊዜ ያለ ማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያረጉ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ በዚህም የተነሳ ለመላእክት አለቃ ለቅዱስ ሚካኤል ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን አጡ፡፡ ዱራታዎስም ሽጦ ለበዓሉ መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ የእርሱን ልብስና የሚስቱን ልብስ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለት፤ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስን ወደ በጎች እንዲሔድና በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ እንዲወስድ አዘዘው፤ ሁለተኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሔዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ አዘዘው፡፡ መልአኩም ወደ ቤት ሳይደርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አስጠነቀቀው፡፡ ወደ ባለ ስንዴም እንዲሔድና የሚሻውን እንዲሁ በእርሱ ዋስትና እንዲወስድ አዘዘው ዱራታዎስም ቅዱስ ሚካኤል እንዳዘዘው አደረገ፡፡
      ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ በረከትን ሁሉ ቤቱ ተመልቶ አገኘው፤ እጅግም አደነቀ፤ የዚህንም የከበረ መልአክ የበዓሉን መታሰቢያ እንዳስለመደው አደረገ፡፡ የተራቡ ድሆችን ሁሉንም ጠርቶ መገባቸውና ወደ ቤታቸው አሰናበታቸው፡፡
SMichael
ከዚህም በኋላ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቅዱስ ሚካኤል ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው ዱራታዎስንም የዓሳውን ሆድ እንዲሰነጥቅ አዘዘው፤ በሰነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሳው ሆድ ተገኘ፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ቴዋብስታን እንዲህ አላቸው፡፡ ‹‹ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ ለባለ ዓሳውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ፤ እግዚአብሔር አስባችኋልና በጎ ሥራችሁን መስዋዕታችሁን ምጽዋዕታችሁን በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፡፡ በኋላኛውም መንግስት ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል፡፡››
በአንድ ዘመን ብዙ ሰዎች ከግብፅ አውራጃ መጥተው ወደ ባሕር ማዶ ሄዱ፡፡ ከባሕሩም በደረሱ ጊዜ በመርከብ ላይ ተሳፍረው ከየብሱ ጥቂት በራቁና ወደ ባሕሩ መካከል በደረሱ ጊዜ ጽኑ ነፋስ ተነሳባቸው ለመስጠም እስኪ ደርሱ ድረስ፡፡
የማዕበሉ ሞገድ እየጨመረ እየጸና ከፍ አለ፡፡ ታላቅም ማዕበል መጥቶ ሊገለብጣቸው ደረሰ፡፡ ፍጹም ጥፋትና ክፉ ሞት እንደ መጣባቸው ባዩ ጊዜ ጽኑ ሐዘን ያዛቸው፡፡ የሚያድናቸው የሚያጽናናቸው አጥተው ተስፋ ቆረጡ፡፡ ያን ጊዜ እንዲህ ብለው ጮኹ፡፡
‹‹የመላእክት አለቃቸው ግሩም ገናና የምትሆን ሚካኤል ሆይ የተአምራትና የይቅርታ መልአክ ነህና፡፡ ልዑል ቸርነቱን የሚገልጥብህ መልአክ ሆይ! እግዚአብሔር ፍቅሩን የሚያስታውቅብህ መልአክ ሆይ ወደኛ ተመልከት እርዳን፡፡ የተጨነቅን እኛን አድነን፡፡ ከመጣብን ሞትና ጥፋት እንድን ዘንድ ስለኛ ወደ ፈጣሪህ ወደ ፈጣሪያችን ወደ እግዚአብሔር ለምንልን፡፡ አሁን የሞት መጋረጃ ዓይናችንን ሸፍኖታልና፡፡ ፍጹም የጥፋት ጥላንም አይተናታልና›› ብለው በፍጹም ልቦናቸው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ በመርከብ ውስጥ ያሉት ሁሉ ጽኑ ለቅሶ እያለቀሱ መራራ እንባ እያፈሰሱ ጮኹ፡፡
ከባሕር ጽኑ ማዕበል ከሞት ያድናቸው ዘንድ ያን ጊዜ በዚያች ሰዓት እግዚአብሔር የልቦናቸውን ሐዘንና ልመናቸውን ሰማቸው፡፡ ያን ጊዜም ይገዳቸው ዘንድ ቸር መልአኩን ሚካኤልን ላከላቸው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወረደ መርከቡን በእጁ ይዞ ሳበው፡፡ በመርከቡ ውስጥ ያሉትንም ወደ የብስ አወጣቸው፡፡ በደኅናቸው ተሻገሩ፤ ክፉ ነገር ጥቂትስ ስንኳ ፈጽሞ አላገኛቸውም፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ገናና የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ፈጽሞ ይጠብቀን፡፡ ከጽኑ ጠላት እጅ በክንፎቹ ጋርዶ ይሰውረን፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡
                        ድርሳነ ሚካኤል ዘኅዳር
ህዳር 8/2007 ዓ.ም
 
የሰው ልጅ በገነት እንደ ቅዱሳን መላእክት በቅድስና አምላኩን በማመስገን በደስታ ይኖር ነበር፡፡ ነገር ግን “ክፉና ደጉን ከምታሳውቀው ዕፀ በለስ እንዳትበላ” ተብሎ የተሰጠውን ትእዛዝ በመተላለፉ ምክንያት ከአምላኩ ተለየ(ዘፍ.3፡6)፡፡እግዚአብሔር በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረው ሰው ክብሩን አጣ፣ ጸጋው ተገፈፈ፣ ፈጣሪውንም አሳዘነ፡፡ ቅዱሳን መላእክትም በእግዚአብሔር መልክና ምሳሌ የተፈጠረው ሰው ከክብሩ ተዋርዶ ሲመለከቱ ተከዙ፡፡

የሰው ልጅ ጠፍቶ እንዲቀር ያልወደደው እግዚአብሔር ወልድ ሰውን ለማዳን ራሱን ዝቅ አድርጎ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሱዋ ነፍስ ነስቶ ተወለደ፡፡ቅዱሳን መላእክትም ከላይ ከአርያም ከአባቱ ሳይለይ እግዚአብሔር ወልድ ሰውን ለማዳን ሲል በግዕዘ ሕፃናት ተወልዶ፣ በእናቱም እቅፍ ሆኖ፤ እንስሳት እስትንፋሳቸውን እያሟሟቁት በማየታቸው ተደነቁ፡፡ ሰውን ለማዳን ሲል ራሱን ዝቅ በማድረግ የባርያውን አርአያ እንደነሣ አስተውለው “ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት፣ ወሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ” (ሉቃ.2፡14) ብለው አመሰገኑት፡፡
ጌታችንም በመስቀሉ የማዳን ሥራውን ሲፈጽም ተጎሳቁሎ የነበረውን የሰው ባሕርይ ወደ ቀድሞ ክብሩ መለሰው፡፡ ስለዚህም እንደ ቅዱሳን መላእክት አምላኩን ለማመስገን እድሉን አገኘ፡፡ (ዮሐ.4፡23)  ነገር ግን ከእነርሱ ጋር በመሆን  ሙሉ ለሙሉ በምስጋና  የሚሳተፈው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ሙታንስ በሚነሡበት ጊዜ በሰማያት እንደ እግዚአብሔር መልአክት ሆነው ይኖራሉ…….” (ማቴ.22፡30) እንዳለው  በትንሣኤ ዘጉባኤ ነው፡፡ እስከዚያ ድረስ ግን በዚህ ምድር ሳለን ከእኛ የሚጠበቅብንን ፣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃል ያስተማረንን፣ በሥራም ያሳየንን ተግባር ተግብረን፣ እንደ ቅዱሳን መላእክት ለአምላካችን በመንፈስና በእውነት በመሆን አምልኮታችንን እንድንፈጽም የእነርሱ ተራዳኢነት በእጅጉ ያስፈልገናል፡፡ ስለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ “መላእክት ሁሉ መናፍስት አይደሉም? የዘለዓለም ሕይወትን ይወርሱ ዘንድ ስለ አላቸው ሰዎችስ ለአገልግሎት ይላኩ የለምን?” (ዕብ.1፡14) ማለቱ፡፡ “የዘለዓለም ሕይወትን ይወርሱ ዘንድ” የተባልነው ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ “እነርሱ በእውነት ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ ስለእነርሱ ራሴን እቀድሳለሁ፡፡ የምለምንህም ስለ እነዚህ ብቻ አይደለም፤ በቃላቸው ስለሚያምኑብኝ ሁሉ ነው እንጂ” (ዮሐ.17፡19-20)እንዳለው በክርስቶስ አምነን ለተጠመቅነው ክርስቲያኖች ነው፡፡

mikealeእናት ልጁዋን እንድትንከባከብና እንድታገለግል ሁሉ ቅዱሳን መላእክትም የዘለዓለም ሕይወትን እንድንወርስ ይራዱናል፡፡ (ሉቃ.13፡6-9) ያለ እነርሱ እርዳታና ድጋፍ በቅድስና ሕይወት አድገን የመንግሥቱ ወራሾች መሆን አይቻለንም፡፡ እንዲህም በመሆኑ በመንፈስ ቅዱስ የልጅነት ጸጋን ከማግኘታችን በተጨማሪ ቅዱሳን መላእክት እኛን ይራዱን ዘንድ ጠባቂ ተደርገው ተሰጥተውናል፡፡ (ማቴ.18፡10)

ቅዱስ ጳውሎስ “እናንተ ግን የሕያው እግዚአብሔር ከተማ ወደምትሆን ወደ ጽዮን ተራራ በሰማያት ወደ አለችው ኢየሩሳሌም ደስ ብሎአቸው ወደሚኖሩ አእላፍ መላእክትም ደርሳችኋል” (ዕብ.12፡22) በማለት እንደተናገረው በክርስቶስ የማዳን ሥራ ከቅዱሳን መላእክት ጋር አንድ ቤተሰብ መሆንን አግኝተናል፡፡ ስለዚህም ጉዞአችንን ጨርሰን ገድላችንን ፈጸመን ለክብር እንድንበቃ ይራዱናል፡፡ በመሆኑም የእኛ ሕይወት በኃጢአት ውስጥ መገኘት ሲያሳዝናቸው፣ በንስሐ ወደ አባታችን መመለሳችን ደግሞ በእጅጉ ያስደስታቸዋል፡፡ (ሉቃ.15፡7) ስለዚህ ስለእኛ በቅድስና ሕይወት ይተጋሉ፡፡ቅዱስ ጳውሎስ "ለራሱ ስለ ሆኑት፥ ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ፥ ማንም ቢሆን ሃይማኖቱን የካደ፥ ከማያምንም ይልቅ የከፋ ነው" ይላል፡፡ (1ጢሞ.5፡8) ስለዚህ እኛ የእነርሱ ቤተሰብ ሆነናልና ቤተሰባዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ሲሉ፣ ደካማው ብርቱን እንዲረዳ ቅዱሳን መላእክትም እኛን ለመርዳት ይተጋሉ፡፡ ነገር ግን የእነርሱ እርዳታ ለእኛ የሚፈጸምልን ተራዳኢነታቸውንና ምክራቸውን የተቀበልን እንደሆን ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እነርሱም እንደ አምላካቸው በእኛ ነጻ ፈቃድ ውስጥ ጣልቃ አይገቡምና፡፡ እንዲህም ስለሆነ የሎጥ ሚስት ምንም እንኳ በመልአኩ እጅ ብትያዝም ለመልአኩ ቃል ባለመታዘዙዋና ለመዳን ባለመፍቀዱዋ የጨው ሐውልት ሆና ቀርታለች (ዘፍ.19፡26)፡፡ በእርግጥ ቅዱስ ጳውሎስ  “በመላእክት የተነገረው ቃል ጽኑ ከሆነ መተላለፍና አለመታዘዝ የጽድቅን ብድራት ከተቀበለ..” (ዕብ.2፡2) በማለት እንደገለጠልን  እግዚአብሔር ለላከው መልአክ አለመታዘዝ ታላቅ የሆነ ቅጣትን ማምጣቱ የማይቀር ነው፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ልጆቹዋ የመላእክትን ተራዳኢነት አውቀው እንዲጠቀሙና የመንግሥቱ ወራሾች ለመሆን እንዲበቁ ስትል ለቅዱሳን መላእክት የመታሰቢያ ቀን በመስጠት በእነርሱ የምናገኛቸውን እርዳታዎች እንዲታወሱ ታደርጋለች፡፡

በዚህም መሠረት በህዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ድምቀት  ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡(ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2  እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)

የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ” (ኢያ.5፡13) ይለናል፡፡


እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነፃ ሲያወጣቸው ይመራቸው የነበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ሹመቱ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይም በመሆኑ ስለ እነርሱ ዲያብሎስ ይዋጋው፣ በጸሎትም ይራዳቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ኃጢአት ሠርተው ሲያገኛቸው ለእግዚአብሔር አድልቶ ኃጢአተኞችን ስለሚቀጣ እግዚአብሔር ሕዝቡን “በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት” (ዘጸ.23፡21)ብሎ አስጠንቅቋቸው ነበር፡፡ ይህም ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙን ያስረዳናል፡፡ ነገር ግን ከላይ የተጠቀሱት ጥቅሶች ሕዝበ እስራኤልን ይራዳቸው የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ አያረጋግጥም የሚል ካለ “መልአክ” የተባለው ቅዱስ ሚካኤል ስለመሆኑ ቅዱስ ገብርኤል ወደ ነቢዩ ዳንኤል በተላከ ጊዜ ገልጦልን እናገኛለን፡- ቅዱስ ገብርኤል በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ቅዱስ ሚካኤል ስለመሾሙ ሲመሰክር “በእውነት በመጽሐፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ፤ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር የሚረዳኝ ማንም የለም”(ዳን.10፡21)ብሎአል፡፡ ስለዚህም ለኢያሱ የተገለጠውና እስራኤላውያንንም የመራው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን እንረዳለን፡፡

የቅዱስ ሚካኤል አለቅነት በሐዲስ ኪዳንም አንደሚቀጥል ይህ ነቢይ በትንቢቱ “በዚያ ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ ሚካኤል ይነሣል..” (ዳን.12፡1) በማለት ተናግሮለታል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ሚካኤል እኛን ከሰይጣን አሽክላና ወጥመድ ይጠብቀንና በጸሎቱ በእግዚአብሔር ፊት ይቆምልን ዘንድ በእኛም ላይ ሹም ነው፡፡ ምክንያቱም እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦችና የርስቱ ወራሾች ነንና፡፡

እግዚአብሔር ነቢዩ ሙሴን የሕዝቡ መሪ አድርጎ መሾሙ እጅግ ትሑትና ስለመንጎቹ ነፍሱን እንኳ አሳልፎ እስከመስጠት ደርሶ ስለሚወዳቸው ነበር፡፡(ዘኁል.12፡3፤ዘጸአ.32፡32) በሕዝቡም ላይ እርሱን መሾሙ እንዲሠለጥንባቸው ወይም እንዲገዛቸው ሳይሆን በትምህርቱና በጸሎቱ እነርሱን እንዲቤዣቸው ነው፡፡ እንዲህም ስለሆነ ቅዱስ እስጢፋኖስ ስለሙሴ ሲመሰክር “እግዚአብሔር ሹምና ቤዛ አድርጎ ላከው”አለ፡፡ (የሐዋ.7፡35) እንዲሁ ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡ ቅዱስ ሚካኤል እጅግ ትሑትና ለሠራዊቱ ተቆርቋሪ የሆነ መልአክ በመሆኑ በመላእክትና በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ተሾመ፡፡ በመላእክትና በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ መሾሙ  ልክ እንደ ሙሴ በእነርሱ ላይ ሊሠለጥንባቸው ወይም ሊገዛቸው ሳይሆን መላእክትን ሊመራ ፣ እኛን ደግሞ ከሰይጣን ጥቃት ሊጠብቀንና በጸሎቱ ሊራዳን ነው (ይሁዳ.12) ፡፡

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን መላእክት እኛን እንደሚጠብቁና እንደሚራዱ እንዲሁም ስለእኛ በፊቱ አንደሚቆሙ ሲያስተምረን“ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ስንኳ እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ሁል ጊዜ በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁ” (ማቴ.18፡10) ብሎናል፡፡ እኛን ይጠብቁ ዘንድ የተሰጡን ቅዱሳን መላእክት ስለእኛ እንዲህ የሚቆረቆሩና ስለመዳናችን የሚተጉ ከሆነ በቅድስናው ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ሚካኤል እንዴት ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ይበልጥ አይቆም? (ሉቃ.13፡6-9) እንዴትስ በተሰጠው ሥልጣንና ኃይል አይረዳን? (መዝ.33፡7) እርሱ “ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው”መባሉም እኛን በጸሎቱና በተራዳኢነቱ የጽድቅ ሕይወታችንን በሚገባ እንድናከናውን እንደሚራዳን የሚያሳይ ኃይለ ቃል ነው፡፡ የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ጸሎቱና በረከቱ በእኛ ላይ ለዘለዓለሙ  ይደርብን አሜን፡