በማለዳ መያዝ ፦ምእራፍ -አንድ 1✿የክፉ መንፈሶች ድርጊት
በስመ አብ
ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ፡፡
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
"የዘመኑንስ ምልክት መለየት አትችሉምን">>ማቴ.16÷3
የክፉ መንፈስ ድርጊት ማለት ፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ፤በሰው አማካይነት ፤ሌሎችን ለመጉዳት
ተብሎ ፤ ከአጋንንት ጋር የሚመሰረትና የሚደረግ ግንኙነት ማለት ነው፡፡ ክፉ መንፈሶች
በሕይወታችን ፣በኑሯችንና በዘመናችን ውስጥ ጣልቃ በመግባት ፤ጉዳት የሚያደርሱ
አደገኞች ይሁኑ እንጂ ፤የእግዚአብሔር አምላክ ጥበቃ እስካለ ድረስ ፤ የጥፋት አቅምና ኃይላቸው ፍጹም ውሱን
የሚሆነው የእምነትና የአምልኮት ጥንካሬ ሲኖር ብቻ ነው፡፡ ዛሬ የክፉ መናፍስቱ ጥቃት ከመቼውም ጌዜ በበለጠ
የተስፋፋና የተመቻቸ ፤ጉዳት የማድረስ ችሎታቸው ፤የዚያኑ ያህል የተጠናከረ ከመሆኑም በላይ ፤የህብረተሰብን ማህበራዊ
አኗኗርን በመለማመድና በመመሳሰል የክፉ መንፈስ ጥቃት የረቀቀ ሥልታዊ ሆኖአል፡፡ ለእነዚህ የሰው ልጆች ጠላቶች
ፍጹም መጠናከር ፤ ከፍተኛ ርዳታና እገዛ ያደረጉት ደግሞ ፤በሚያስገርም ሁኔታ ፤ ራሳቸው ሰዎች ናቸው ፡፡ እንዴት ?
እስቲ ሁሉንም በዝርዝር እንመልከት ፦
<<እግዚአብሔር የደሚወዱትን ሁሉ ይጠብቃል ፤>> መዝ.144(145)20 1.1 የዛር መንፈስ ፤
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
ዛር የሚባለው ከዘር የተወረሰ ፤ከዘር የመጣ ፤በዘር የሚሄድ ማለት ሲሆን
፤ትርጉሙም ፤ለሰው ዘር ተመሳሳይ ተፈጥሯዊ ባህርይ ያላቸው ሁሉ ፤በዘር ውስጥ ማለፋቸውን የሚያሳይ ምልክት
ነው፡፡የዛር አጋንንትና ሰይጣን በቤተሰብ ውስጥ ሲመለክና ሲገበር ቆይቶ ፤ከአምላኪዎቹ የሚወለዱት ልጆች ሁሉ
፤መንፈሱ አብሯቸው ተወልዶና አድጎ ፤መጨረሻ ላይ ፤የኔ ዘር ናቸው በማለት በኃይል ያርፍባቸዋል፡፡ በዚህ ረገድ
ዲያቢሎስ ልዩ የሆኑ በአራት የተከፈሉ ዕቅዶች አሉት ፡፡
☞የሰውን ሕይወት ሙሉ ለሙሉ
መቆጣጠርና መምራት ፤የሚሔድበትን አቅጣጫ መለየት ፤
☞በከፍተኛ ፍጥነትና ግፊት ዕቅዱን ተግባራዊ ማድረግ ፤ ☞የጥቃት አድማሱን ማስፋፋትና መገምገም ፤
☞ለጊዜው በአጥቂነት የሚጠቀምባቸውን ሰዎች መሳሪያዎቹ በማድረግ ፤የኢኮኖሚ አቅም ማጎልበት ፤ክብርና ዝናን
ማጎናፀፍ ፤ሌሎች ብዙዎች የሚጠፉበትን መንገድ ማመቻቸት እና በተግባር መፈጸሙን ማረጋገጥ ነው፡፡
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት
የሳጥናኤል እቅዶች ሲሆኑ በአፈጻጸም ሂደት ውስጥ ለሰብአዊ ፍጡር መረጃ እንዲያገኝ ምንም አይነት ፍንጭ አይሰጥም
፡፡ የክፉ መንፈሶች የገሐዱ ዓለም ላይ በተጨባጭ ገጽታ አለመታየታቸው ብዙዉን የሰው ልጅ የትውልድ ህልውናን
ሲፈታተኑ፤ ከመኖራቸውም በላይ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የሰጠውን ተስፋ ክብር ጸጋና በረከትና ምገስን እንዳያገኝ
ለመፋለም የራሳቸውን ክፋትና ጥፋት መፈጸሚያ በማድረግ ሲጠቀሙበት ኖረዋል፡፡ይህንንም በቃየን ሕይወት ማየት
ይቻላል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን የዛር ምልክት ለመጀመሪያ ጊዜ የታየውና ለዘር
መበላሸት ምክንያት የሆነው ሰው ፤ ቃየን ነው፡፡ ቃየን ማለት ፤ከእብራይስጥ ቋንቋ ወደ አማርኛ ሲተረጎም
፤የጦር አበጋዝ ማለት ነው፡፡
የአቤልና የቃየን መስዋዕት በእግዚአብሔር ፊት
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
" እግዚአብሔር ወደ አቤልና ወደ መስዋዕቱ ተመለከተ ፤ ወደ ቃየንና ወደ መስዋዕቱ
አልተመለከተም ፡፡" ዘፍ .4÷4-6 ቃየን እጅግ ተናደደ ፤ፊቱም ጠቆረ ፡፡ እግዚአብሔርም ቃየንን አለው
፤"ለምን ተናደድህ? ለምንስ ፊትህ ጠቆረ? መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን
ኃጢአት በደጅህ ታደባለች ፤ ፈቃድዋም ወደ አንተ ነው፡፡ ግን በእርስዋ ንገስባት፡፡" አለው፡፡በዚህ
የእግዚአብሔርን ቃል ውስጥ የተገለጸት ፤ ኃጢአት ታደባለች፡፡ ፤ፈቃድዋ እና በእርስዋ ንገስባት የሚሉት ሦስት
ቃላት የሚያመለክቱት ፤የሴት ጾታን ነው፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ፤ቃየን የሴት ዛር አጋንንትን በጥፋት መንገድ
እርሱንና ትውልዱን ትመራ ዘንድ ነገሠችበት፡፡
የቃየን መስዋዕት የስስት ፤ የንፉግነትና እግዚአብሔር ን የማይፈራና የማያመልክ
መሆኑን ዲያብሎስ ስለአወቀ ፤እርሱን ለክፋት ፤ለቅናት ፤ለንዴትና ለፊት ማጥቆር እርግማን በመሳሪያነት መግለጫው
በማድረግ ምድራዊ የኃጥያት አሰራርና ምት በይፋ መንገድ አገኘ፡፡ በዚህ የተነሳም ፤ ንጹህ ወንድሙን አቤልን
አለምንም በደል ፤ በጥላቻና በልበ ቂመኘነት ተነሳስቶ ፤ በድንጋይ ወግሮና ደሙን አፍስሶ ገድሎታል ፡፡
ስለዚህ የቃየን መንፈስ ፤የደም አፍሳሽነት ወይም የግድያ ወንጀል ጀማሪ በመሆን ፤ ዲያብሎስን የሰው ልጅ ዘር
አጥፊነትን በገሐዱ አለም ያለ እድሜ መሞትን ማሳያ በማደረግ ተጠቀመበት ፡፡ደጉ፣ ብሩኩና ቅዱሱ ሰው አቤል
በአምልኮቱ ምክንያት ምተ፡፡ አሁን መስዋዕቱን እግዚአብሔር የሚቀበለው ሰው የለም፡፡ ለአምልኮት ክብር የሚሰጠው ሰው
በአጠቃላይ አምላክ የወደደው ሰው ፤ አቤል የለም፡፡ለምድር የቀረው በሕይወት ያለው ቃየን ነው፡፡
ወንድሙን ያሳደደ፤ ደሙን
ያፈሰሰ ፤በድንጋይ ወግሮ የገደለ፣የተረገመው ቃየን አለ፡፡ቅናት ፣ተንኮል ፣ክፋትና ምቀኝነት መሠረታዊ በመሆን
ዕድሉን ያገኙት፤ለመጀመርያ ግዜ በቃየን ሕይወትና ዘመን ውስጥ ነው፡፡
አዳም ከገነት መሸሽ ፣መራቆትና መደበቅ በነበረው አስፈሪና
አሳዛኝ በሆነው ሂደት ላይ የቃየን ተግባር ወንድሙን በመግደል ሲጀመር ለቀጣዩ ትውልድ የግድያ አስተማሪነቱ
ለዲያብሎስ አላማ ልዩ መርሆ ሆኗል፡፡
ይህ አለም ቃየንን ይወዳል ፡፡በዚህ ምድር ስትኖር ፤ስትወጣ ፣ስትገባ ፣ስትሰራ
፣ስትማር ፣ስታገኝ ፣ስትደሰት ሁሉ በመንገድህ ላይ ፤ከግራ ፣ከቀኝ ፣ከኀላ ፣ከፊት ፣ከላይ ፣ከታች ሳይቀር ፤የቃየን
መንፈስ አለ፡፡
የእግዚአብሔር ቃልና የቃየን ድምፅ
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
<<እግዚአብሔርም ቃየንን አለው ፤ወንድምህ አቤል ወዴት አለ? እርሱም አለ ፤ አላውቅም ፤ የወንድሜ
ጠባቂ እኔ ነኝ? አለው ፦ምን አደረገህ? የወንድምህ የደሙ ድምፅ ከምድር ወደኔ ይጮሀል ፡፡አሁንም የወንድምህን ደም
ከእጅህ ለመቀበል አፏን በከፈተች ምድር ላይ አንተ የተረገምህ ነህ፡፡ምድርንም ባረስህ ግዜ እንግዲህ ሀይሏን
አትሰጥህም፡፡በምድር ላይ ኮብላይና ተቅበዝባዥ ትሆናለህ፡፡>> አለው ዘፍ.4÷9
<<እግዚአብሔር ተናግሮአልና ሰማያት ስሙ ፣ምድርም አድምጪ ልጆችሽን ወለድሁ ፤አሳደግሁም ፣እነሱም
አመፁብኝ፡፡>> ት/ኢ.1÷2
በአዳም፣ ሔዋንና በተተኪው ትውልድ ውስጥ የዲብሎስ አስተሳሰብ ጅማሬ
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
ንዴት ፦የጠብ መጀመሪያ አባት እንዲሆን በቃየን ሕይወት ዲያብሎስ ከመገለጹ በላይ ፤በወንድሙ ላይ የፊት
ማጥቆርና የመቀየር ገጽን የአካል ክፉ ጠባይ ጽንሰ ሀሳብ የሚታይበት ሆኖ ቃየን እንዲገለጥ አድርጎታል ፡፡ በቃየን
ሕይወት የተጀመረው ቅናት ፣ ንዴት ፣ክፋት ፣ተንኮል ፣ ምቀኝነት ፣ግፍ ፣ ቁጣ ፣ብስጭት ፣ቂም እና በቀል
እነዚህ ሁሉ የዲያብሎስ ሀሳቦች እስከ ዛሬ ድረስ በሰው ልጅ ልብ ውስጥ መሠረታዊ የኑሮ አካል ሆነው ከመገኘታቸው
በላይ ፤ ለዘመናት የሰው ዘርና ተፈጥሮን ሲያበላሹ የቆዩ የዲያብሎስ መርሆዎች ናቸው፡፡
በቃየን የተጀመረው
የፊት ማጥቆር ጠባይ ዛሬም ብዙ ሰዎች ክፉ መንፈስ በውስጣቸው ሲኖር ይሄው ችግር ሙሉ በሙሉ ይከሰታል፡፡ ፊታቸውና
ቋንቋቸዉ ይለወጣል ፣ይናደዳሉ ፣ይቆጣሉ ፣ ይራገማሉ ፣ያማርራሉ ፣ መንፈሱ ከተገለጠ ደግሞ ፣ ያጓራሉ ፣ወይም
በጣም ይጮኸሉ፡፡ ግልፍተኞ በሆኑ ጊዜም የሚያደርጉትን ስለማያውቁ ፣ቤተሰብንና በቅርብ ያለውን ሁሉ ሊጎዱ ይችላሉ
፡፡ደም ካላዩ የማይረኩና የማይበርዱ ይሆናሉ፡፡ ቃየንም ፣ጊዜያዊ እርካታ ያገኘው ወንድሙን ከገደለ በኀላ ነበር፡፡
የደም ፍርድና የግድያ ዛር
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
በቃየን የተጀመረው የግድያ ውሳኔ ለዲያብሎስ የጥፋትና የሞት አሠራር ዋና ግብ አድርጎት ፣የሰው ልጅን ወደምት
የመምራት ስልጣን የማግኘቱ ውጤት አንዱ መንገድ ሆኖአል፡፡ ቃየን ወንድሙን የሚያስገድል መንፈስ ያዘው ፣ ደምን
የሚያፈስ ፣ደም ማየት የሚወድ ከአዳም ቀጥሎ ሁለተኛ የኃጥያት የግድያ ወንጀል ጀማሪ እንዲሆን ሰይጣን ተጠቀመበት
፡፡
ስለዚህ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ደም ማየት የሚፈልጉ ዛሮች የሰውን ልጅ
በመቆራኘት ፣በዓለም የህብረተሰብ ባሕል ውስጥ በተለያየ መንገድ የደም መፍሰስ ፍላጎትን አዳበሩ በእንስሶች በዶሮ ፣
በበግ የሚረጋጉ ዛሮች በአገራችን ሰፊ ቦታ ነበራቸው፡፡ ያ ሂደት ተቀይሮ በምድራችን ላይ ለዘመናት ያልተቋረጠ
የጦርነት ደም ሲፈስ መኖሩ የዛሮቹ ዕድገት መሳያ አንዱ ምልክት ነው፡፡ በአሁኑ ዘመን ያሉ ዛሮች የቀድሞ
ጠባያቸውን ለቀው ዘመናዊ የአጠቃቀም ሥልት በመያዝ ሲማሩ መማር ፣መሪ ሲሆኑ አብሮ መሪ መሆን ፣በሥልጣን
፣በማዕረግና በሀብት አለመርካት የመሳሰሉ ጠንቆችን ሥር የሰደደ ባሕርይዎች እንዲሆኑ በማድረግ ለክፉ ተግባራቸው
መገልገያ አድርገውታል ፡፡
ከማለዳ በዓመፅ ታሪክ ውስጥ መኖር
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
የዓመፅ ጅማሬ ታሪክ ሲነሳ፣ የቃየን መንፈስ በአመፀኝነት የፈጸመው የግፍ ግድያ ተግባር ፣ብዙ ደም በዓለም ላይ
ላፈሰሱ ፣ግጭቶች የመጀመሪያው አባትና አስተማሪ መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ ካለፉት ብዙ ዘመኖች ውስጥ በዓለማችን
ዙሪያ የተካሄዱ ጦርነቶችና እልቂቶች የዓመፃ ግፍ የአፈጻጸሙ ማሳያ ሆነው ፣ለአሁኑ ዘመን ትውልድና ርዕዮተ -ዓለም
የሞት ማገናዘቢያ የጥፋት ልጅ ሆነው፣ዛሬ የሚረግሙት ፋሽስቶችና ናዚዎች በመባል እየታወሱ የጥላቻ ታሪክ
ማንጸባረቂያ ሆነዋል ፡፡ በቃየን ዘሮች ውስጥ የተከሰተው የጦረኝነትና የጦር መሣሪያ ፍልስፍና ዛሬ አድጎ ወደ
አቶሚክ ደምሳሽ ቦንብና ወደ ኑክሌር የጨረር ሞት የሰው ልጅ መድረስ፣ዲያብሎስን ለጥፋት ዓላማው የላቀ እርካታ
እንዲያገኝ አግዞአል፡፡ሌላው የቃየን ዘር መንፈስ ፣ወንዝን ተከትሎ መኖርንና ፣የወንዝ ውኃ መንፈስን ማምለክ
፣መጠየቅና ማማከር ፣ከወንዝ አጋንንት ጋር መዳበልና መዛመድን የጀመረ ትውልድ ነው ፡፡ይህን ሂደት ለዲያብሎስ
በሰው ልጅ ልብ ውስጥ ውጣውረድና ዓመፃ እንዲመሰረት ረድቶታል ፡፡ ስለዚህ የ21ኞው ክፍለ ዘመን ትውልድ የሰይጣን
የክብረ በዓል ቀንን ያከብራል ፡፡"ሐሎይ" በመባል የሚታወቀው የሰይጣን ቀን ዓለማቀፋዊ በዓል እንዲሆን አንዳንድ
አገሮች ወስነዋል ፡፡ስለዚህ አሰላለፉ ፣ሰይጣን ሰው ሰይጣን ሆኖአል ማለት ነው፡፡ የቃየን የመጀመሪያ ዓመፅ በብሉይ
ኪዳን ውስጥ አልፎ ፣በአዲስ ኪዳን ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስን በመስቀል ፤ሐዋርያትን በማሳደድና በመግደል ፣ከዛም
ቤተክርስቲያንን በማቃጠልና ክርስቲያኖችን በመውረር ፣ጣዖታትን በማምለክ የነበረው የከሃዲነት መንፈስ አድጎ ፤ዓለም
የዓመፃ ዘመን ላይ ደረሰ፡፡
ሰው እጅ ላይና ዲያቢሎስ ላይ የወደቀ ትውልድ
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
አቤል ያለእድሜው በወንድሙ እጅ ላይ ወድቆና ተወግሮ ደሙ ፈሶ ሞተ፡፡ በዚህም ዘመንና
ጊዜ ብዙ ሰዎች ፤ የአገር መሪዎችን ጨምሮ ፤በሰው እጅ ላይ ወድቀው መገኘት ፤የተለመደ ችግር ሆኖአል ፡፡በስራ
፣በእውቀት ፣ በሥልጣንና በመርሐ-ግብር ፣በርዕዮተ ዓለም ጫና ፣በኢኮናሚና በተመረዘ የአስተሳሰብ ተጽእኖ ሥር
መያዝ ወቅታዊ ክስተት ሆኖ ይገኛል ፡፡
የችግሩ አጣብቄም የፈቃደኝነት ግዴታና የግዴታ
ፈቃደኝነት ውስጥ የመግባቱ ጠባይ ከሕልውና ጋር የተያያዘ እንዲሆን ገና ከማለዳ ክፉው መንፈስ የሚያዘጋጀው ሴራና
ተንኮል እንደሆነ የዘመኑ ሳይንስ አልተረዳውም ፡፡ከዚህ ገጎን የማቴሪያልና የስነ-ጥበብ አምልኮት የዘመኑን ሊሕቃን
በፍልስፍና ውስጥ እንዲደበቁና የማይታየውን የክፉ መንፈስ ዓለም እንዲዘነጉት በማድረግ ዲያቢሎስ ልዩ ሚና ተጫውቷል
፡፡ ብዙ የዓለም ምሁራኖች በግሪክ ሥነ-ቃል ተዋጽዖ የሳይንሳዊ ስያሜ ላይ ዕድሜያቸውን ጨርሰ ውና እምነት
አልባ በመሆን ፤ በነፍሰ ሕይወት ተዋርደዋል፡፡ በጤናና በሕክምናውም ረገድ ተመሳሳይ ብዙ ስሕተቶች በዲያብሎስ በኩል
ተተግብሯል፡፡እንግዲህ በዓለም ላይ ያለዉ ችግር ከመነሻው ብቻ ሳይሆን ከመድረሻዉ ላይ የክፉ መንፈስ ውስብስብ
ፈተናና በሳይንስ የማይፈታ ችግር ሆኖ ይኖራል ፡፡
በቃየንና በዘሩ ውስጥ የኃጢአትና የሞት ንግስት ዛር ✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿~
"መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚያበራ አይደለምን ? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች ፤ፈቃድዋም ወደ
አንተ ነው፤አንተ ግን በእርስዋ ንገሥባት፡፡ቃየንም ወንድሙን አቤልን ፤ና! ወደ ሜዳ እንሂድ አለው፡፡ሜዳም ሳሉ
ቃየን በወንድሙ በአቤል ላይ ተነሳበት ገደለውም፡፡" ዘፍጥረት .4 ፥7-8
ዛሬ መላውን ዓለምና የሰው ዘር ትውልድን እያናጋው ካለዉ ክፉ መንፈሶች አንዱ ፤የሴት ዛር
የአያያዝ እሽቅድድም እየተጠናከረ መምጣቱ ነው፡፡
በቃየን ልብ ውስጥ ንግሥናን ያገኘችው የኃጥያት ዛር የሴት
አጋንንትና ሰይጣን፤የሴትና የወንድ ግብረ-ሰዶማውያንን (የሌዝብያንና የሆሞዎችን)መብት ሕጋዊ የጋብቻ አካል እንዲሆን
በማድረግ ፤ብዙ የክርስቲያን ልጆች ፤ልብና ሕይወት አግኝታለች ፡፡
አሰላለፏን ዘመናዊ
በማድረግ እንደ ትውልዱ ጠባይና አስተሳሰብ ሥልቷን በመለዋወጥ ፤ትውልዳችን በክፉ አመልና ሱስ ከእምነትና ከአባቶቹ
የሃይማኖት ሥነ-ምግባር እንዲ መጣ በማድረግ፡ ከክህደት ርዕዮት ውስጥ ወደ ኃጢአት ምት በመምራት ላይ ትገኛለች
፡፡
ከማለዳ መበላሸት
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
ቃየን በኃጢአት
ላይና ሀጢያት በቃየን ላይ ከነገሰች በሁዋላ ኮብላይና ተቅበዝባዥ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል ፡፡ዛሬ
የእያንዳንዱ ቤተሰብ ልጆች ፤በዚች የኃጢአት ንግስት ከማለዳው ስለሚያዙ የራሳቸው ፍላጎትና አስተሳሰብ እየመሰላቸው
በክፉ መንፈስ በሚከተሉት መንገድ ይመራሉ፡፡ ለምሳሌ
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ተማሪዎች ፤በሱስ መንፈስ ለመያዝ በጣም የቀረበና የሰፋ ዕድል ያላቸው ሲሆን
፤ይህንኑ ክፉ የሱስ መንፈስን የሚያስፋፋ ፣የንግድ ቤቶች በየትምህርት ቤታቸው መግቢያና መውጫ በር ላይ ገበያቸውን
በማደራጀት ፤ወጣቱ በዘመናዊ የጥፋት ሥልት ውስጥ እንዲገባ አድርገዋል ፡፡
ከመነሻው አዲሱን ተተኪ ትውልድ ከትምህርት ቤት ደጃፍ እየተቀበሉ ከሚያሰናክሉና ከሚያበላሹ የጥፋት መንገዶች መካከል ጥቂቶቹን እንመልከት ፤☞
♦እንሞክረው ፤እንየው ፤ለጥናት ጥሩ ነው በማለት ፤ጫት አብሮም ሲጋራ ፤በመቀጠልም ሺሻ ፣ሐሺሽ ፣መጠጥ
ወዘተ...ይጀምራል ፡፡
♦ከአደንዛዥ ዕጾች በተጓዳኝ ፣የወሲብ ፊልምችን በጋራና በተናጠል በመመልከት ፤የኃጢአት ንግሥቷ ዛር
በውስጣቸው ቤትዋን ትሠራለች፤
♦የኃጢአቷን ንግስትየሚያበረታቱ ዘፈኖች ፤ከወሲብ ቀስቃሽ አለባበስ ጋር በመታጀብ ፤ልቅ
የሆነ ጠባይ እንዲወርሱ ያደርጋል ፡፡ ♦የሚያስፈሩና የሚያሰቅቁ (ሆረር) ፊልምች ውስጥ ፣ደም የሚመጡ የሰው
ፍጡሮችን ፣ቤት ፣መንገድ ፣ ንብረት ፣በፈንጂና በሮኬት ፣በአውሮፕላን ድብደባ ሲወድም ፣የሰው ሕይወት በአሰቃቂ
ሁኔታ ሲያልፍና አካሉ ሲጓድል በማሳየት ፤ዕድሉን ከፊልሙ ጋር እንዲያያዝ አድርገው እያደር የወደፊቱ እጣ ፈንታው
በመንፈሱ ወይም በመንፈስዋ እንዲወሰን መንገድ ይጠርጋል ፡፡ከዚህ በኋላ
ትውልዱ ጥፋትን አይቶና ተምሮ በመንፈሱ ተገዶ ክፋትን ቢሰራና ቢፈፀም ፤የሚያስቆጭና የሚያስገርም አይሆንም
፡፡ ሌሎች ተመሳሳይ የጥፋት መንገዶችም እንደቀልድና እንደ ዋዛ ፤ከዘመናዊነት ውስጥ በመመንጨት ፣ትውልዱን ወደ
ተበላሸ አቅጣጫ ሲወስዱት ብዙ ጊዜ ተስተውሏል ፡፡ይህ ሁሉ የመናፍስቱ ድርጊትና የጥቃት ሥልት መሆኑ በአንክሮ
ሊታወቅ ይገባል ፡፡ ♦በኃጢአት ንግስት ዛር የተለከፉ ሰዋች ሁሉ ፤ያዩትንና የሰሙትን ፣ያደረጉትንና
የፈፀሙትን ፣ወደ ማዕረግ እና ወደ ሥልጣን በማዉጣት ፤ከመልካም ነገር ይልቅ ፤ክፋትን በማበረታታት ፤ክፉዋንና
ክፉውን መንፈስ የሚጠቅሙ አገልጋዮች ይሆናሉ ፡፡
♦ በዚህ ክፍለ ዘመን ያለው ትውልድ ፤ከትምህርትና ከእውቀት
ጋራ በተያያዘ ሁኔታ ከሚገጥሙት ፈተናዎች መካከል ፤በኢንተርኔት ላይ ያለ ስራ ተጎልቶ በሚጨርሰው ሰፊ ጊዜ
የተነሳ ፤በዓይን የሚያርፉ የሱስ መንፈሶች በላቀ ሁኔታ እየተጠቃ የመገኘቱ ሁኔታ አንዱ ነው፡፡
እነዚህ
በኢንተርኔት ማለትም በምስጢራዊ የአጋንንት አምልኮት ስር የሚለቀቁ የመንፈሱ የአስተሳሰብና የክህደት
፤ዘዴዋች፤የሳይኮሎጂ ፤የስሜት ፤የወሲብ ፤የአስትሮሎጂ ፣ወዘተ....ተዋጽኦዎችን በሙሉ የ ሚያጠቃልሉ ሲሆን
፤በምንሰጣቸው ከፍተኛ አትኩሮት እና ተመስጦ የተነሳ የሚገቡ መንፈሶች ናቸው ፡፡ብዙ ጊዜ በኢንተርኔት ላይ ያለ
ተጨባጭ ስራ ተጎልተው የሚያሳልፉ ሰዎች፤ልክ እንደ ካርታ ሱስ ውለው ቢያድሩበት አይሰለቹም ፡፡አንዳንዶች ውለው
እንዳደሩበት ምን እንዳዩ እንኳን ሲጠየቁ ፤አስታዉሰው ለመናገር ያዳግታቸዋል ፡፡
✿በዚህ በኢንተርኔ ሱስ
የተለከፉ ሰዎች ፤በሳይንሳዊ ትንታኔ ሕብረተሰቡንና ቤተሰባቸውን ግራ በማጋባትና በማስቸገር ፤ሌሎችን ከእምነት
ጎዳናና አንባ ለማስወጣት፤በንቀት ቋንቋ የሚናገሩ፣የሚተቹ፣የሚቃወሙ፣የሚያፌዙና አዋቂ ሆነው ለመቅረብ
የሚጥሩ፣በአጠቃላይ፤ክፉው መንፈስ የሚመላለስባቸው ማደሪያው ይሆናሉ ፡፡
ይህ የሚያመለክተን፤ክፉ መንፈሶች
የዘመኑን የእውቀትና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን በመጠቀም፤በረቀቀ ጥበብ፣ከእግዚአብሔር መንገድእንዴት እነደሚያርቁ፣የሞትና
የነፍስ ጉዳት በማድረስ ላይ የሚገኙ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን፤ኢንተርኔትን ጨምሮ ሌሎች
የቴክኖሎጂ ውጤቶች በሙሉ፤ማለት ሳይሆን በዚህ ረገድ ኃጢአትን የሚያበረታታውን ፤ነዉርና ከሞራል ሥነ-ምግባር
የወጣውን፣በአጠቃላይ ክፉ መንፈስ የሚመራውንና ከእግዚአብሔር ሕግ የወጣውን፤በተለይ በኢንተርኔት የሚለቀቁትን
የክፉ መንፈስ መልዕክቶችን አሉታዊ ተፅእኖ ለማመልከት ነው፡፡በአጭሩ፤ኢንተርኔት የሚጠቅመንን ያህል፤በዚህ መንገድ
ከተጠቀምንበት ደግሞ፤ሊጎዳን እንደሚችል የሚጠረጠር መሆን የለበትም፡፡ የሚፈውስ መድኃኒት እንዳለ ሁሉ፤የሚገድልም
መድኃኒት አለ፡፡ብርሀን እንዳለ ሁሉ ጨለማም አለና !፡፡
እንዲህ አይነት ችግሮችን በዘመናዊ መንፈስ ተጽእኖ
ያዳበሩ ሰዎች ባሉበት አካባቢና መንደር የሚወለዱ ልጆች፤ወላጆቻቸውን ጨምሮ፤ጭንቀት፤መረበሽ፤የልብ መደንገጥ፣እንቅልፍ
መጣትና መቃተት፣ጠብና ሳያውቁት መነጫነጭ፣መበሳጨትና ግልፍተኛ መሆን፣እቃ መስበር፣መግዛትና ደግሞ መስበር፣በድርጊቱ
መርካት፤የባልና ሚስት መለያየት መበጣበጥና መጯጯህ፤ሌሊት ሳያውቁት በር ከፍቶ መውጣት፣ገንዘብን ከቦርሳ አውጥቶ
መጣል፣ቀንመደበትና ሌሊት መንቃት፣ሞትን መፈለግና በተቃራኒው ማማረር ወዘተ............መንፈሱና ሰዎቹ ያሉበት
አካባቢ መለያ ባሕርይ ነው፡፡
በአካባቢው የሚወለዱ ልጆች ጠባይ
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
በአብዛኛው ቅብጥብጥ፣ትምህርት የማይወዱ፣የአመጋገብ ፍላጎታቸው የተዘበራረቀ፣አንድ ጊዜ ከአቅም በላይ የሚበሉ
ሲሆን፤በሌላ ግዜ ደግሞ ምንም የማይቀምሱ፣ስማቸውንም ቤተሰባቸውን የሚረሱ፣ደንታ የሌላቸው፣መፍዘዝና ግራ መጋባት
የሚታይባቸው፣እንዲሁም እሺን የማያውቁ ሁል ግዜ የአፍ መፍቻቸው እንቢ ወይም ኖ(NO)ብቻን
የሚናገሩ፣የማይታዘዙ፣የማይደፈረውን የሚደፍሩና የማይናቀውን የሚንቁ፣በአንጻሩ ደግሞ፤የሚናቀዉና የሚደፈረው
የሚከብዳቸው፤ተቃራኒ ጠባዮች የሚስተዋልባቸው ይሆናሉ ፡፡
ፊልም ማየት የሚወዱ፤ለብቻቸው በህልም መንፈሱ ወሲብን ሲያስተምራቸው የሚያዩ፤ገለልተኛና ብቸኝነት የሚመቻቸው ሆነዉ፤ከነበረው ትውልድ ወጣ በማለት በአካልና በአስተሳሰብ የተለዩ ሆነው ይወለዳሉ ፡፡
ቃየንና የቃየን ቤተሰብ ውጤት
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
የቃየን ንፉግና በረከተ-ቢስ፣ፍቅር አልባና ፣የአስተሳሰብ ክፉነት ለራሱና ለትውልዱ ብዙ መዘዞችን አስከትሏል ፡፡
♦በቃየን ሕይወት ውስጥ ትልቁ ችግር የፍቅር መንፈስ ማጣትና አለመገለጥ ነው፡፡ለጠብና ለተንኮል፣ግፍና ግድያ ወዘተ... ለመሳሰሉት የወንጀል ጀማሪዎች መከሰቻ ሆኖአል ፡፡
♦ፍቅር መልክ የሚይዘውና ውበት የሚያገኘው ሁል ግዜ ከእግዚአብሔር ንጹህ አምልኮት ጋር ሲሆን ብቻ ነው፡፡ከዚህ
እውነት ከወጣ ግን ፍቅር ሚዛኑንና አቅጣጫውን በመሳት፤የመዘበራረቅ ዕድሉ እጅግ የሰፋ ነው፡፡በቃየን ሕይወት ውስጥ
የታየው ፤ፍቅር፤ የጦርነት የዘፋኝነትና ከቦታ ቦታ መንከራተት፣ የወንዝ ውሀ መንፈስ የተጀመረበት ፣ የባዕድ
አምልኮትና የኃይል ኑሮ ትውልድ የበቀል ሞት አስተማሪ በመሆን የአሳቹን መንፈስ አገልግለዋል ፡፡
♦በዚህም
፤አስተሳሰብ ፤ገሐዳዊውን ዓለምና የባለ አስተሳሰቡን ሕይወት ፣ኑሮና ትውልድ የሚወስን እንደሚሆን ከቃየን መገንዘብ
እንደሚቻል ግልጽ ነው፡፡ ቃየን በወንድሙ ላይ በጥላቻ በመነሳት የውስጥ አስተሳሰብ ሂደት ያመጣው ውጤት ፤ ወደ ክፉ
አምርቶ ፤ሽፍትነትን ፣ውንብድናን ፣ስደተኛነትን ፣ኮብላይነትና ክዳትን እንዲሁም ፤ከእግዚአብሔር እምነትና አምልኮት
የራቀ ትውልድ ጠባይ እንዲሆን ዓይነተኛ ገጽታ ሆኖ እየኖረ ነው፡፡ ለክፉ ተግባር በመነሳሳት ግፊት ውሰጥ ክፉው
መንፈስ በአዳም ልጅ በቃየን ላይ ዕድል በማግኘቱ ፤ጥፋትን ለመግለጥ ተጨማሪ መነሻ መንገድ እንዲያገኝ ረድቶታል ፡፡
የቃየን ገጸ ባሕርይ ለክፉው ዓለም
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
ዛሬ በዓለም ላይ ካለው የንፉግነት የውስጥ አስተሳሰብ በብዛት ተከስቶ የሚታየው በእግዚአብሔር ስም
የሚደረጉ ክንውኖች ናቸው፡፡ እነዚህም በጎነት ማጣትና የእምነት ዋጋን ከነ ጭራሹ በመተው ፤በመርሳትና በመዘንጋት
መካከል በሕልውና ውስጥ የበረከት ጅማሬ በአምላክ እንዳይመጣ ማገጃ እንቅፋት ከመሆኑም በላይ ፤የኑሮ ተስፋና
የትውልድ ሰማያዊ ሥጦታ ላይ ሁለንተናዊ እጦትን እንዳመጣ በቃየን ሕይወት መማር ይቻላል ፡፡
ቃየን ለእግዚአብሄር የአምልኮና የክብር መስዋዕት ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆነ ፤የመጀመሪያው ንፉግ ሰው በመሆን
፤የጉልበቱ ዋጋ በእምነት መስዋዕት በኩል አልተገለጠም ፡፡ስለዚህ ቃየን በየትኛውም ትውልድ ላሉ ንፉግ ሰዎች ምሳሌ
በማድረግ ፤ዲያብሎስ የመቅኖ-ቢስነትን አኗኗር በዓለም ላይ ገልጦበታል፡፡
የበረከትን ጣዕም አለማወቅ
በሰው ልጅ ዘር ውሰጥ አንድ ብሎ የጀመረው በቃየን ሕይወት ውስጥ ነው ፡፡ ቃየንና ዘሩ ዕድሜያቸው ያለቀው በረከትን
ለማግኘት በራሳቸው ዘዴና ጥበብ ሲፈልጉ ፤ በምድር ላይ ኮብላይና ተቅበዝባዥ በመሆን ፤ዕድል አግኝተዋል ፡፡
በእግዚአብሔር ያልተጠበቀ በረከት ፣ፍላጎትና ተግባር ፣ያልተቀደሰ ትውልድ ምልክቱም እነደ ቃየን በመንፈሳዊ ሕይወት መቅበዝበዝ መሆኑን ለዓለም ምልክት የጥፋት አርዓያ ሆኖአል ፡፡
የካደው ትውልድ ቋንቋ
✿✿✿✿✿✿✿✿✿
"አላውቀውም ፤የወንድሜ ጠባቂ እኔ ነኝን" የሚለው የቀደመው ቋንቋ በዚህ ዘመን
ይንጸባረቃል፡፡ ጾም ጸሎት አላውቅም ፤የአባቶቻችንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ታሪካቸውን እንዲሁም ተጋድሎአቸውን አላውቅም
፤እኔ የነሱ ጠባቂ ነኝን? የሚለው የቃየን ቃል ፤ዛሬም ይሰራል ፡፡
ይህ የዛር እልህ
፣የደም እርግማን ፣የወንጀል ጩኸት ፤የአሁኑ ዘመናችንን እያሳየና በግልፅ እየመሰከረ ነው፡፡ጻድቃንና ቅዱሳንን
አላውቅም የሚለው የመናፍቁ መንፈስ አንዱና ዋናው የዚህ የካደው ትውልድ ቋንቋና መግለጫ ነው፡፡
የቃየን መሸበር ፤
✿✿✿✿✿✿✿
"ቃየንም እግዚአብሔርን አለው ፦ኃጢአቴ ልሸከማት የማልችላት ታላቅ ናት ፡፡እነሆ ዛሬ ከምድር ፌት
አሳደድኸኝ ፤ከፊትህም እሰወራለሁ ፤በምድር ላይ ኮብላይና ተቅበዝባዥ እሆናለሁ ፤የሚያገኘኝም ሁሉ ይገድለኛል ፤
"አለ፡፡
መላው ክርስቲያኖች ሁላችንም ፤ማስተዋልና መገንዘብ ያለብን ፤የዛሬ አብዛኛው ስራችንና ግብራችን ከሀጢአት ነጻ ስላልሆነ ይህ ድምፅና ኡኡታ ፤የቃየን ብቻ አለመሆኑ ነው፡፡
አሁን አቤል የለም ፤የማይራራውና "አላውቅም ፤የወንድሜ ጠባቂ እኔ ነኝ?"ያለው ቃየን ነው፡፡ ዛሬ
ቃየን በሕይወት ባይኖርም መጥፎ ድርጊቱ እየተወራረሰ አሁን ድረስ በምደባር ላይ ነግሦአል፡፡ዛርን መውረስ ማለት ይህ
ነው፡፡ የቃየን ዘር፤የጦርና የሙዚቃ መሳሪያዎች ጥበብ ከጦርነትና ከወንዝ አምልኮት ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ
የተከሰተበት ፤ደም አፍሣሽ ነገድ ነው፡፡የእርግማኑም ቃል ፤
"ቃየንን ሰባት እጥፍ ይቀበሉታል ላሜሕን ግን ሰባ ሰባት እጥፍ፡፡"ዘፍጥ ፤4÷24 ይህ የጦርነትና የደም ዛር ነው፡፡
"ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል ፡፡" ማቴ 16÷4
የአካባቢ ሥሞችንና የሰዎችን መጠሪያ፤የወረሱ የዛር የንግስና ሥሞች
❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀
በደጋና በበረሀ የወደቁት የአጋንንትና የሰይጣን የዛር መንፈሶች የሰዎችንና የአካባቢ ስሞችን እየወረሱ፤በሰዉ ዘር ላይ የተሾሙ ናቸው ፡፡
ዛሮች በተለያየ አካበቢዎች የተለያዩ ስያሜዎን የያዙ ይሁኑ እንጂ ፤በያዙት ሰዉ ላይ የሚያሳድሩት ተጽእኖና ጉዳት በአብዛኛው ተመሳሳይ ነው፡፡
በአገራችን ከሚገኙ የዛር የንግሥና ስሞች መካከል ፤ሙጨ ዘሪጋ ፣አዳኝ ወርቁ ፣ሐጎስ ፣ጎለም እሸት
፣ጨንገር ፣ሰይፉ ጨንገር ፤የሚባሉት የዛር መንፈሶች በዋናነት የሚወዱት ግብር ፣እንሾሽላ ፣ወርቅ ሽቶ ፣በተመሳሳይ
ሰከት ቡና ማፍላት ፣ጌጣጌጥ ፣በጣም የደመቀ ቀለም ያለው ልብስ መልበስ ፣ዘፈንና ከበሮ መምታት ነው፡፡
ጠቋር ፣አዳል ሞቲ ፣ወሰን አጋጅ ፣ወሰን ገፊ ፣ወሰን ራሔሎ ፣ሻንቂት ፣ሻንቆ ፣ ሃደ ሐሮ ፣ሃደ
አባይ ፤አባ መጋል ፣ሼህ አንበሶ ፣ነቢ ጅላሌ ፣ብር አለንጋ ፣ገውዘ ላዝም ፣ሻንቆ አባዲና ፣አርዱላ ፣99 መሊካ
፣ሞቲ አረቢያ ፣ግራኝ አባ ጉግሳ ፣አላቲ ፣ሪሣ ፣ኦፋ አቡኮ ፣ ኦፋ ጨፌ ፣ ኦፋ ለገሰ ፣ ኦፋ ደመና ፣የታዬ
ከራማ ፣የአሩሲዋ እመቤት ፣ቡሎ ገርቢ ሣማ ቀልቢ ፣ አርሜት ፣ድማሜት ፣ሙሄት ፣አብድር ቃዲር ፣ዋቅ ፣ቦዥና ጨሌ
፣የወሎ ክብሪት ፣ቤሩድ ፣ሼህ ወልይ ፣የጠረፏ ንግስት ፣አዬ ሞሚና ፣አቴቴ ዱላ ፣አውሊያ ከራማ ፣አውሊያ ሼክ ሁሴን
፣ጅላሌ አብዱል ቃድር ፣ ተኮላሽ እያሱ ፣በረኸኛ አጋንንቶች ማለትም ፤ወሰን ገፊ ፣ አዳኝ ሱማሌ ፤ ቆሌ አዳኝ
የልክፍት ዛር ፣ቦረንትቻ ፣አሞር ፣ ውቃቢ ፣ወዘተ.......የንግሥና ስሞች ናቸዉ፡፡
የመናፍስቱ ሥያሜ ፣ ሥምሪትና ጥቃት ፤በዋነኛነት ሥያሜያቸውን ባገኙበት አካባቢ አይሎ የሚገኝ ቢሆንም ፤በተለያየ
ምክንያቶች ሰዎች ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወራቸው የተነሣ ፤በሰሜን ያለው መንፈስ ፤ በደቡብ ፤በምዕራብ ያለው ፤
በሰሜን ፣ በመሐል ያለው በምስራቅ ወዘተ...ሊኖር ይችላል ፡፡
የዛር መንፈሶች ለሰዎች የሚያወርሱዋቸው አጠጠቀላይ ጠባያት
✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿✿
በየሰአቱ የሚቀያየር ጠባይና የተደበቀ ስውር ሰው መሆን ፤ውስጥ ውስጡን መሸመቅ ፤እልኸኝነት ፣ወይም ከሚገባው
በላይ ግልጽ መሆን ፤ብዙውን ጊዜ በንዴት በብስጭት ጊዜውን ማሳለፍ ፣በር ዘግቶ በጨለማ መቀመጥ፣ ለብቻ ማልቀስ
፣ወሬ ማናፈስ ፣ ነገር ከያዘ አለመልቀቅ ፣ የአመል ግትርነት ፣የእግዚአብሔር ሰዉ መጥላት ፣ ማሳደድ ፣ ደምን
ማፍሰስ ፣ ደም ሲፈስ ማየት ፣ ተበቃይ ፣ ቂመኛ ፣ አመፀኝነት ፣ መጋደል ፣ ሌላውን በክፉ አይን ማየት ፣
በተለይም በሌላው ኑሮና አምልኮት ፣ በእግዚአብሔር ጸጋና ሞገስ መቅናት ፣ በሌላው እድገት ፊትን ማጥቆር ፣ ስም
ማጥፋት ፣ መተቸት ፣መቃወም ፣ ማፌዝ ፣ መሳደብ ፣ መራገም ፣ሐሜት ፣አሽሙር ፣መራራ ቃል መናገርና እንደሱስ
መሆን ፣በገንዘብ ፣በሥልጣንና በጉልበት መሳሪያነት መተናኮል ፣ለሌላው ውድቀትና ሞት መመኘት ፣ለማጥፋትና ለማውደም
መቸኮል ፣የሌሎችን ኪሳራና ውድቀት በማየት መደሰት ፣ሃይማኖት መለዋወጥና የእምነት አለመኖር ፤
ወዘተ...የመሳሰሉት ሁሉ ፤ዛር ያለባቸው ሰዎች የተለመዱ ጠባያት ናቸዉ ፡፡
የዛር መንፈሶች በአብዛኛው
ተመሳሳይ ጉዳት የሚያደርሱ ቢሆንም ፤በዋነኛነት ግን ፤ ከማሕፀን ጀምሮ ለልክፍት የሚሆኑ ፣ የሰው ልጆችን ፤
ከርታታ ፣ባካኝ ፣ሰርቶ መና የሚያደርጉና የመከራ ኑሮን የሚያወርሱ ናቸው፡፡
የዛርና የውቃቢ የውርስ
መንፈሶች ፤ሌሎች ወደ ሰዎች የሚላኩ የዲያብሎስ መንፈሶችን ፤በመሳብና በፍጥነት ተቀብሎ ቦታ ሰጥቶ በማስተናገድ ፤
በውስጣችን ሰይጣንን አሰባስቦ በማደራጀት ሰፊ ጠባያቸውም ፤ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱን አዳኝ ወርቁ
የተባለውን መንፈስ ፤ በምሣሌነት እንመልከት ፡፡
አዳኝ ወርቁ
✿✿✿✿✿✿
መልካም መዓዛ ያለው ሽቶና እጣን ፤ ከጌጣጌጥ ወርቅ በብዛት የሚወድ ሲሆን ፤ መልክና ውበት ያላትን ሴት
ከሌላ ወንድ አስቀድሞ ለራሱ እንደ ሚስት ስለሚይዝ ፤ የዚህ መንፈስ ሰለባ የሆኑ ብዙ ሴቶች ባል አያገቡም ፤
አይፈልጉም ፡፡
ስለዚህ የባል ፍቅርን ሳያዩ ፣ ልጅም ሳያምራቸው ፤ የቤተሰብ ኃላፊነት ሳይሰማቸው
ቀርቶ ፤ ዘመናቸውን ከመንፈሱ ጋር ይጨርሳሉ ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ፤ ልጅ የመውለጃ ዕድሜያቸው ካለፈ በኋላ
በተቃራኒው ፤ መንፈሱ በውስጣቸው ልጅ መውለድ እንዲያምራቸውና ፤ እንዲጓጉ በማድረግ ፤ የቁጭት ስሜት ያሳድርባቸዋል
፡፡ በዚህም የተነሣ ፤ ውስጥ ውስጡን እየተብከነከኑና ፤ በመካንነታቸው እያዘኑ ፤ ፈጣሪ አምላካቸውን እያማረሩ
እንዲኖሩ ያደርጋቸዋል ፡፡ የክፉው መንፈስ ዋንኛ አላማ ፤ ሰዎች በሕይወታቸው እግዚአብሔርን እንዲያማርሩ ስለሆነ ፤
በዚህ በኩል የሚያደርገው እንረቅስቃሴ የተቃና ይሆንለታል ፡፡
የአዳኝ ወርቁ ዛር ጠባይ ፤ ሴት
ልጁን ያኳኩላል፣ ወርቅ በጸጉርዋ ፣ በአንገትዋና በጆሮዋ ፣በእግርዋና በእጅዋ ላይ ያበዛል ፡፡ ራሱም ልዩ ውበት
የመስጠት ኃይል ያለው ሲሆን ፤በገሃዱ ዓለም ያለ ሌላ ወንድ ሲጠጋት ወይም ሲያያት ይማረክባታል ፤ የሩካቤ ፍላጎትም
እንዲሰማው ያደርጋል ፡፡ ይሁን እንጂ ፤ በአብዛኛው ሴቲቱ ከወንድ ጋር ለመሆን አትፈልግም ፡፡
መንፈሱ ከብዙ ወንዶች ጋር የሚያገናኛት ቢሆንም ፤ ከሁሉም ጋር አያግባባትም ፡፡ ምክንያቱም ፤ ደም ስለሚፈልግ ፤ ከሁለቱ አንዱን ወይም ሁለቱም በማጋጨት ብሎም ለማጋደል ስለሚፈልግ ነው፡፡
ባለጸጋዎችን ፣ ሾፌሮችን እና ነጋዴዎችን ወዘተ...በመጥለፍ ገንዘባቸውን ይሰልባቸዋል ፡፡ልባቸው ላይ
መልኳንና ውበቷን ያስቀምጣል ፡፡ እስኪያገኟትም ድረሰ ፣እንቅልፍ ይከለክላቸዋል ፤ ይረብሻቸዋል ፡፡ አንዳንዶቹ
እስኪያብዱ ድረስ ይፈትናቸዋል፡፡
ይህ እንግዲህ መንፈሱ ሴቲቱን በሃብት ለማበልፀግ የሚሄድበት መንገድና ለኃጢአት አሰራሩ የሚጠቀምበት ዘዴ ነው፡፡
እንዲህ ዓይነትዋ ሴት አንዱን ቀን ፤ ለተማረከባት ፣ ሀብቱን ላፈሰሰባት ወንድ ስትሰጥ ፤ ሁለት ወይም
ሶስት ቀን ደግሞ የመንፈሱ ተራ ይሆናል ፡፡ ይህ ፤ ከመንፈሱ ጋር የምትገናኝበት ጊዜ መሆኑ ነው ፡፡
በዚህ ወቅት ዕጣን ፣ ሉባንጃ ፣ሽቶ የመንፈሱ አልባሳት ሁሉ ሳይቀር ይዘጋጃል ፡፡ የሚጠይቃቸው የግብር
ዓይነቶች ሁሉ ከተሟላ በኋላ ፤ በነጋታው ገንዘብ የሚያፈስላትን ሰው ያዘጋጅላታል ፡፡ የሰውየውን አቋም ፣
ተክለ-ሰውነት ፤ መልክና ውበቱን ፤ በሕልሟሙዋ አስቀድሞ ሊጠቁማትም ይችላል ፡፡
ሌላው ጠባዩ
፤ዓይን ለዓይን በመተያየት ፣ በድምጽ (በስልክ ውስጥ የመሚደረግ ንግግርን ይጨምራል ) ፣ሰላምታ በመጨባበጥ ፤
በልብስ በመነካካት ወዘተ...ሁሉ ሳይቀር ፤ የፍትዎት ስሜትን ያነሣሣል፡፡
በአብዛኛው ከተለመደው የተፈጥሮ ባሕርይ ወጣ ያለ የወሲብ ስሜትን ሚፈጥረው ክፉ መንፈስ መሆኑን ብዙዎች አይገነዘቡትም፡፡
ለምሳሌ ፤ አስገድዶ የመድፈር ጠባይ ፤ የዚህ የዝሙት መንፈስ አንዱ አካልና መገለጫ ነው፡፡
ለመለያየት የሚጠቀምበት ዘዴ
✿✿✿✿❀❀❀❀✿✿✿✿❀❀❀❀
ከጊዜ በኋላ ሴቲቷን የተጠጋው ፤ ሰው የማያቋርጥ ከባድ ራስምታት ፤ ሆድ መንፋት ፣መደበት ፣ ማስጨነቅ ፣በመሳሰሉት አስቸጋሪ ጠባያት፤ አማሮ ሊያባርረው ይችላል፡፡
የተለያየ አካላዊ አደጋም ያበዛበታል ፡፡ ጠቋርን የመሰለ ዛር ከሆነ የግሞ ፤ ከቅናቱ የተነሳ ፤ሕይወቱን
ሊያጠፋው ሁሉ ይችላል ፡፡ ሌላው በመንፈሱ የመገለጫ ጊዜ ፤ ለእርስዋ በመኝታ ላይ ልታየውና ልትዳስሰው እንዲሁም
፤ ሌሊት ክንድዋ ልታገኘው ትችላለች፡፡
በዚህ መንገድ ብዙ ሴቶች የመንፈሱን ሩካቤ ያፈቅራሉ ፡፡ከባል
ጋር ግንኙነት ባያደርጉ ፈቃዳቸው ነው፡፡በተለያየ ምክንያት ግንኙነት ቢፈጽሙ እንኳን እርካታ አይኖራቸውም ፡፡በዚህ
ግንኙነት የሚፈጠሩ ልጆች ጀግም ፤ በተፈጥሮና በአስተሳሰብ የተጎዱ ሆነው ይወለዳሉ ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ፤የቡዳ
መንፈስ አስተላላፊዎች በመሆን ፤የሌሎችን ሕይወት ይጎዳሉ ፡፡
ይሁን እንጂ አንዳንዶቹ ፤
ከተኙበት ሲነቁ ግን ፤ አቅፈዉ የተኙትን መንፈስ ገጽታ ፤ በዓይነ -ሕሊናቸው ሲያስታውሱት ፤ከባድ መንፈሳዊ
ቀውስ ውስጥ በመግባት ፤ ከፍተኛ የሆነ ፍርሀትና ጭንቀት እንዲሁም ሽብር ውስጥ ይገባሉ ፤ ይወድቃሉ ፡፡
በተለይ ይህንን ሁኔታና ሥቃያቸውን ለሌላው ሰው ለመንገር ሥለሚያሳፍራቸው ፤ ውስጣቸው እንደቆሰለ ይኖራሉ
፡፡"ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ፤ ነፍሱንም ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል ? ወይስ ሰው ስለነፍሱ ቤዛ ምን ይሰጣል ?"
ማቴ. 16÷26
ሾተላይ የዛር የመተናኮል የውርጃ መንፈስ ፤
✿✿✿❀❀❀✿✿✿❀❀❀✿✿✿❀❀
ብዙ ጊዜ እንዲህ አይነት ዛር ሾተላይ በመሆን ፤ እርግዝና ላይ አደጋ የመፍጠር ችሎታ የሚኖረው ሲሆን ፤ተተኪ
ትውልድን በማጨንገፍ የሚረካ ፤ የሰው ደም በማፍሰስየሚደሰትና የቤተሰብን ሐዘንና ለቅሶ ፤በልጅ ማጣት መቸገራቸውን
እያየ እንደ ድል የሚቆጥር ፤ ስውር እልኸኞ የዛር መንፈስ ነው፡፡
የዛር መንፈስ ከማህጸን ጀምሮ ያለው፤ ሌላ ጥቃት ፤
✿✿✿❀❀❀✿✿✿❀❀❀✿✿✿❀❀❀✿✿
ከማሕጸን የሚወረሱ የዛር መንፈሶች ፤ የእናትና የአባት የመንፈሰ ጉዳቶች በዋናነት ያስከትላሉ ፡፡
ሀ. መካን(መኻን) ማድረግ
ለ. በሚወለዱት ሕጻናት ላይ ፤ የአእምሮም ፣የጤና፣እንከንና የአካል ጉዳት መፍጠር ለምሳሌ ፤፦የዛር መንፈስ
አንዳንድ ሕጻናትን የአካል ጉዳተኛ ፣ የአእምሮም ዘገምተኛ ወዘተ...ከማድረጉ በተቃራኒው ፤ ያለዕድሜ ደረጃቸው
እንዲያስቡና ሥራቸው ሁሉ ፤ እንደ ትልቅ ሰው እንዲሆን ያደርጋል፡፡
ብዙ ጊዜ እንደነዚህ አይነት ሕፃናት ፤ አስተሳሰባቸው ፤ እድሜያቸው ከሚሸከመው በላይ ስለሚሆን ፤ ረዥም ዓመት በሕይወት የመቆየት ዕድላቸው የመነመነ ነው፡፡
ሐ. የሚወለዱትን ልጆች ባሕርይ ማበላሸትና መጥፎ ጠባይን ማውረስ ፤
መ. ያለዕድሜ ፤ተፈጥሯዊዉን የወር አበባ ዑደትን ማዛባት ፤ ማለትም✿ ፤ ሴት ሕፃናት ገና ለአቅመ ሔዋን
ሳይደርሱና ጡት ሳያወጡ ፤ በስምንትና በዘጠኝ ዓመት ዕድሜያቸው በሚያስደነግጥ ሁኔታ የወር አበባ እንዲያዩ ያደርጋል
፤
✿ ሴት እህቶች ደግሞ ፤ ባልተለመደና በማይጠበቅ ሁኔታ ፤በአብዛኛው በሰላሣና በሰላሣ አምስት ዓመት ፤
እንዲሁም አስከ አርባ ዓመት ዕድሜ ክልል ላይ ሲደርሱ ፤ የወር አበባ ማየት እንዲያቆሙና ያለጊዜያቸው እንዲያርጡ
ያደርጋል፡፡
✿ አንዳንዶቹም በዚሁ መንፈስ ጥቃት ተነሳ ፤ ከሃያ ዓመት ዕድሜያቸው ጀምሮ ፤ ለአንድ ወይም
ለሁለት ዓመት ፤ወይም ከዚያም በላይ ለሚሆን ጊዜ ፤ ወር አበባቸውን ሊያጠፋው ወየይም ሳያዩ እንዲቆዩ ሊያደርግም
ይችላል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ በአንድ ወር ውስጥ በተደጋጋሚ የወር አበባ እንዲፈሳቸው ያደርጋል ፡፡
በሕክምናው በኩል ሐኪሞች እንደሚገልፁት " እንደዚህ ዓይነት ክስተቶች አዲስ አይደሉም ፡፡በተለያየ ምክንያት
አልፎ አልፎ ሊፈጠሩ ይችላሉ ፡፡ ሆኖም ፤ በብዙ ሴቶች ላይ የመታየቱ ጉዳይ ግን ፤ ያልተለመደና ራሱን የቻለ ጥናት
የሚያስፈልገው ነው፡፡" ይላሉ ፡፡
ነገር ግን ፤ በርካታ ሰዎች ከላይ የተገለፁት ችግሮችና
እንከኖች በአንድ በኩል በዲያብሎስ ምሪት በክፉ መንፈሶ ተፅዕኖም ሊመጣ እንደሚችል ፤ ገና መረጃው የላቸውም
፡፡በተደጋጋሚ እንደተገለጠው ፤ ዲያብሎስ በዛር መንፈሶች በኩል ከሰዎች ጋር አብሮ እየተወለደና እየተወራረሰ ፤ ዘሬ
አድርጌያቸዋለሁ እያለና መንፈሱን ከማሕፀን ጀምሮ እያስቀመጠ ፣ ከፍ ብሎ የተጠቀሱትን ጉዳቶች የሚያደርስ ቢሆንም ፤
በእግዚአብሔር መንፈስ የሚሸነፍና ወደ ሲኦል ወርዶ የሚታሰር ጠላት መሆኑን ለአፍታም ያህል ፤ መጠራጠር የለብንም
፡፡
ለምሳሌ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በማርቆስ ወንጌል 9÷29 "ይህ ወገን በጸሎትና በጦም ካልሆነ
በምንም ሊወጣ አይችልም " ይላል ፡፡ ይህ ማለት ወገን ሆኖ አብሮት ስለተወለደ በአካላዊ ተፈጥሮው ላይ ደንቆሮና
ዲዳ በማድረግግ የእናቱና የአባቱ ሕልውና እንደጎዳ መመልከት ይቻላል ፡፡
☞ሴት ዛር በወንድ ላይ ስትኖር ፤ የምታመጣው ጉዳት
❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀
ሴት ዛር ወንድን በምትይዝበትና አብራ ተወልዳ በምታድግበት ወቅት ፤ ሕይወቱን ትለማመድና ልክ እንደሴት ልጅ በመቀመጫው በኩል በየወሩ የወር አበባ እንዲመጣበት ታደርጋለች ፡፡
ይህ ፈፅሞ ያልለተለመደ ሁኔታ በሕክምናው በኩል፤ የአንጀት ጉዳት ወይም የኪንታሮት ችግር መስሎ
እንዲታይ፤ መንፈሱ ማሳሳቻውን ያቀርባል ፡፡ምንም ይባል ምን፤የሚገርመው ግን፤በሰውየው ላይ የወር አበባ ዑደቱ ልክ
እንደሴቶች ቀን እየጠበቀ ለዓመታት ያህል ያለማቋረጥ የመታየቱ ጉዳይ ነው፡፡
ይህ የተዛባ ተፈጥሮ ፤የዛር መንፈስን የሚያመልኩና የሚገበሩ ሰዎች የበዙበት አካባቢ በሚገኙ ቤተሰቦችና ማህበረሰብ ውስጥ በስፋት የሚገጥም ክስተት ነው፡፡
☞ዝብረቃ
✿❀✿❀✿❀
በማይጠበቅ ሁኔታ ድንገት አስደንጋጭ የሆነ ቃል፤በንግግር መሐል ላይ ዝብርቅ ማድረግ የተለመደ የዘመናችን ስልጡን
ሕብረተሰብ ዋና ችግር ነው፡፡ይህ፤ የዛር መንፈስ ሌላው ጥቃት ነው፡፡ዝብረቃ በሁለት መልኩ ይከሰታል፡፡
ሀ.☞የተሰወረ ዝብረቃ ፤
✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀
የመንፈሱ ሚስጥራዊ አሰራር በሥራ፣ በትምህርት ፣በንግድ ሥራና ሙያ በዕቅድና በፖሊሲ ንድፈ ሐሳብ እንዲሁም
በጸሎት ጊዜ ሁሉ ጣልቃ በመግባት፤ አደገኛ ነገርን የሚያመጣ የመሪዎችና የኃላፊዎች የዝብረቃት ዕዛዝን
ጨምሮ የዓለማችን ትልቁ በሕይወታችን ውስጥ የሚገኙ የመንፈስ ውጥረት ነው፡፡
ለምሳሌ ዘብረቅ ያለ ዳኛም ይሁን መሪ ቶሎ ከእስር ቤት ሃምሳ ሰዎች ይረሸኑ ብሎ ከተናገረ ፤ ሰውየው ሳያውቀው በዝብረቃ መንፈስ ሃምሳ ሰዎች ተገደሉ ማለት ነው፡፡
በሕክምናውም በመድኃኒት ምርምሩም በተለያየ ኃላፊነትና የሥልጣንና የማዕነግ እርከን ያሉ ሰዎች ላይ የጦር መሪዎችንም ጨምሮ እስካልተወሰነ ሰዓት ድረስ ፤ የዝብረቃ መንፈስ ያጠቃቸዋል ፡፡
ለ. ☞ግልጽ ዝብረቃ ፤
✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀
ከፍሬ ነገሩ ጋር የማይገናኝና የማይያያዝ ሐሳብማስገባት ፣በጨዋታ መካከል ከመልካም ሥነ-ምግባር
የወጣና የወረደ ቋንቋ መጠቀም ፣ መሳደብ ፣ ማዋረድ ፣ወይም ማልቀስ ፤በተቃራኒው ፤ ከልክ በላይ መሳቅ ፤በሙሉ
ሰውነት ድንገት ብድግ ብሎ መዝለልና ወዲያውኑ የመቃተት ድምፅ ማሰማት ፣በእጅና በከንፈር ለብቻ ማውራት ፣ቁጭ ብሎ
መዋተት ፣ሰዎችን ያለስማቸው አጠገባቸው ባለ ሰው ስም መጥራት ፣ ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን አለስማቸው መጥራት ፤ለምሳሌ ፤
እንጀራ ለማለት ፤በቆሎ ፣ውኃ ለማለት ፤ እንጨቱን አምጣና እንጠጣ ወዘተ.....ሁሉ ማለት ፤ የዚዙ ክፉ መንፈስ
የሚታይና የሚሰማ የዝብረቃ አካል ነው፡፡
ያለ ዕድሜ መጃጀት
✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿
የዛር መንፈስ ከሚያስትለው ጉዳቶች መካከል ፤ ያለ ዕድሜ መጃጀት ፣ መርሳትና ሠዘንጋት አንዱ ነው፡፡ ይህ
፤ በተለይ በአሁኑ ዘሠን ትልቅ ችግር ሲሆን ፤ ጥቃቱን በብዛት የሚያሳርፍባቸው ፤ ሳይንቲስቶች ፣ፖለቲከኞች ፣
ምሁራኖችና በኃላፊነትና ስልጣንና ማዕረግ የሚገኙ ሰዎች ፣ ሴቶችን ጭምር መርሳትና መዘንጋት ከክፉው መንፈስ አንዱ
መሰረታዊ ችግር ነው፡፡
በሕክምናው (ዲያሜንሺያ) ብለው ስም ስለሰጡት ፤ በሳይንሳዊ ስያሜው መንፈስነቱን መደበቂያ ምሽግ አድርጎታል ፡፡
ለጸሎት ፣ ለአምልኮትና ለእግዚአብሄር ቃል ጊዜና ቦታ የሌላቸው ሁሉ ፤ በዚህ ክፉ መንፈስ ይጠቃሉ ፡፡
☞መሰረታዊ ምልክቶቹ ፤
❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿
☞ያወጡትን ዕቅድና ፕሮግራም መርሳት፣ወይም ሐተው፤
☞ከሕሊናቸው ዕውቀታቸውና ልምዳቸው መጥፋት ወይም መሰወር ፤
☞ገንዘባቸውንና ንብረታቸውን አለመቀቆጣጠር ፤
☞ከቤታቸው ወጥተው ፤ የሚኖሩት መንደር ፣ መንገድና መኖሪያ ቤታቸው ጠፍቶአቸው ሌላውን ሰው እስከ መጠየቅ መድረስ፤
☞ምሳ ወይም እራት በልተው ፤ አልበላሁም ብለው መጣላት፣ ማኩረፍ ፣ መናደድና መጮኽ ፤
☞ሚስታቸውንና ልጆቻቸውን መርሳት ፤ አለ ዕድሜ በዚህ መንፈስ የመጠቃት ልዩ ምልክቶች ናቸው፡፡
☞አዋቂው ሰው እንደ ሕጻን መሆን
✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀
ከዚህ በተቃራኒው ፤ የዛር መንፈስ በዕድሜ ከፍ ያሉና የገፉ ሰዎችን ፤ እንደ ሕጻን እንዲያስቡና እንዲሰሩ
በማድረግ ፤ መካሪና አስታራቂ በመሆኛ ዕድሜያቸው ፣ እንዲሁም ጧሪና ቀባሪ በሚያስፈልጋቸው ሰዓት ፤ እንደ ልጅ
አድርጎ ቅሌትና ውርደት ውስጥ ይከታቸዋል ፡፡
☞ሾፌሮችንና ተሳፋሪዎችን በመንገዳቸው ላይ የሚያጠቁ ክፉ መንፈሶች
✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿❀✿ይቀጥላል .
Saturday, 23 April 2016
ሰሙነ_ሕማማት
የሰሙነ_ሕማማት_ትርጓሜ_ና_ክንዋኔና_ሚስጢር
ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከገባ ጀምሮ ያሳለፈውና ከትንሳኤው በፊት ያለው አንድ ሳምንት " የመጨረሻ ሳምንት " ተብሎ ይጠራል፡፡ በሌላ አጠራር ደግሞ " ሰሙነ ሕማማት " ይባላል፡፡ በጌታ ላይ የሞት ምክር የተመከረበትና በብዙ መከራና ሕማማት የተገደለበት ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህም ሰሙነ ሕማማት የሚለው ስያሜ ጌታ የተቀበለውን ፀዋትዎ መከራን ለማዘከር የሰጠ ስያሜ ነው፡፡ የጌታ የመስቀሉ ሕማሞች ወይም " ሕማማት መስቀል " ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦
ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ከገባ ጀምሮ ያሳለፈውና ከትንሳኤው በፊት ያለው አንድ ሳምንት " የመጨረሻ ሳምንት " ተብሎ ይጠራል፡፡ በሌላ አጠራር ደግሞ " ሰሙነ ሕማማት " ይባላል፡፡ በጌታ ላይ የሞት ምክር የተመከረበትና በብዙ መከራና ሕማማት የተገደለበት ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህም ሰሙነ ሕማማት የሚለው ስያሜ ጌታ የተቀበለውን ፀዋትዎ መከራን ለማዘከር የሰጠ ስያሜ ነው፡፡ የጌታ የመስቀሉ ሕማሞች ወይም " ሕማማት መስቀል " ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦
1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀል በችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።
በዚህ ሳምንት ውስጥ ካህናትና ምዕመናን በአፀደ ቤተ ክርስትያን ተሰብስበው ከሀጥያት ርቀው ከምግብና ከመጠጥ ተቆጥቦ በጾምና በጸሎት የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ ሲያዜሙ ግብረ ሕማም የሚባለውን መጽሐፍ እያነበቡ ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ።
ከአባታችን አዳም በደል ወይንም ስሕተት በኋላ በሕማማት፣ በደዌያት፣ በመቅሰፍታት፣ ወዘተ በብዙ መከራ የሰው ልጅ ሊኖርባቸው ግድ የሆነባቸው ዘመናት ጥቂቶች አልነበሩም፡፡ ጥሮ ግሮ ወጥቶ ወርዶ ለፍቶ ማስኖ የዕለት ጉርስ የቀን ልብስ ማግኘት እጅግ አዳጋች ነበር፡፡ ሁልጊዜ የሰው ልጅ ቢያጠፋ ቢበድል ከሕገ እግዚአብሔር ቢወጣ እንኳ የዋህ፣ ታጋሽ፣ ቸር፣ አዛኝ የሆነ አምላክ የጠፋውን ሊፈለግ የተራበውን ሊያጠግብ የታረዘውን ሊያለብስ፣ ፍቅር ያጣውን ፍጹም ፍቅር ሊለግስ፣ ሰላም ለሌለው ፍጹም ሰላም ሊሰጥ፣ ተስፋ የሌለውን ተስፋ ሊያጐናጽፍ ከሰማይ ወረደ፤ ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ ቀንና ሌሊት ጾመ፡፡ በጾሙም የኃጡአት ሥሮች ወይም ራሶች የተባሉትን ስስትን፣ ትዕቢትንና ፍቅረ ንዋይን ድል አደረገልን፡፡ እኛ እርሱ የጾመውን ጾም እንድናከብር እንድንጾም ምሳሌ ሆነን፡፡ ዲያብሎስን ድል አድርጐ ድል እንድንነሣው ኃይልና ምሳሌ ሆነን፡፡
#ሰሙነ_ሕማማት_ምንድን_ነው?
ሰመነ ስምንት /ሳምንት/ አደረገ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ከዕለተ ሆሣዕና ሰርክ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ያለውን ጊዜ ወይም ቀናት የሚያመለክት ነው፡፡ ሐመ ማለት ታመመ ማለት ሲሆን ይህም የሰውን ዘር ሁሉ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ ለማውጣት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ የተቀበላቸውን ጸዋትወ መከራዎች የሚያሳስብ ነው፡፡ ዕለታቱ የዓመተ ኩነኔ ወይም የዓመተ ፍዳ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት፣ የሚያለቅሱበት፣ የሚሰግዱበት ቤት ንብረታቸውን ትተው ከሌላው ቀናትና ጊዜያት በተለየ መልኩ ቤተ ክርስቲያናቸውን የሚማጸኑበት፤ ጧት ማታ ደጅ የሚጠኑበት፤ ኃጢአታቸውን በቤተ ክርስቲያን አደባባይ ለካህኑ የሚናዘዙበት በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ሳምንት ነው፡፡
በዚህ ሳምንት ብዙ አዝማደ መባልእት አይበሉም፤ ይልቁን በመራብ በመጠማት በመውጣት በመውረድ በመስገድ በመጸለይ በመጾም በየሰዓቱ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጸዋትወ መከራዎች በማሰብ አብዝቶ ይሰገዳል፡፡ መከራውን፣ ሕማሙን፣ ድካሙን የሚያስታውሱ ከቅዱሳት መጻሕፍት ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ መዝሙረ ዳዊት ግብረ ሕማማት ወዘተ በየሰዓቱ ይነበባል፡፡
#መስቀል_መሳለም_የለም፡፡ ካህናትም እግዚአብሔር ይፍታህ አይሉም የሳምንቱ ሥርዓተ ፍትሐት አይደረግም፡፡ ይኸውም ይህ ሳምንት ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገርንበት ከጨለማ ወደ ብርሃን የተጓዝንበት የመሸጋገሪያ ወቅት ምሳሌ በመሆኑ ነው፡፡ በዕለተ ምጽአት መላእክት የመለከት ድምጽ በማሰማት የዳግም ምጽአትን ዕለት ለማሳሰብ ምእመናን ጥሪውን ሰምተው ለዚህም አስቀድመው ተዘጋጅተው የበዓሉ ታዳሚዎች መሆናቸውን በማጠየቅ በዚህ ሳምንት ዲያቆኑ ቃጭል እየመታ በየሰዓቱ ምእመናኑን ያሳስባል፡፡
#በሰሙነ_ሕማማት_የሚገኙ_ዕለታትና_ስያሜያት
#ዕለተ_ሰኑይ /ሰኞ/
ይህ ዕለት አንጾሖተ ቤተ መቅደስ /የቤተ መቅደስ መንጻት/ እና መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ /ማር.11-11፣ ማቴ.21-18-22 ሉቃ.13-6-9/፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ «ወመሰለ ሎሙ ወይቤሎሙ አሐዱ ብእሲ በለሰ ቦቱ ውስተ አጸደ ወይኑ ወየሐውር ይንሣእ ፍሬሃ ወኢይረክብ ...»፤ ይህንም ምሳሌ አለ ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም፡፡ በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡
#ዕለተ_ሠሉስ /ማክሰኞ/
ይህ ቀን ጌታችን ሰኞ በተናገረውና ባደረገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀረቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማረበት ዕለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የጥያቄ እና የትምህርት ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ ጥያቄውም ጌታ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት ለጸሐፍትና ፈሪሳውያን ይኸውም ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?» የሚል ነበር፡፡ /ማቴ.21-23-27/፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ «ወይቤሎሙ ኢየሱስ አማን እብለክሙ ከመ መጸብሓውያን ወዘማውያት ይቀድሙክሙ ውስተ መንግሥተ እግዚአብሔር»፤ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው እውነት እላችኋለሁ ቀራጮችና ጋለሞቶች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመግባት ይቀድሙአችኋል ሲል አስተምሯል፡፡ /ማቴ.21-28/
#ዕለተ_ረቡዕ/እሮብ/
ይህ ዕለት ደግሞ የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚችሉ ምክር የጀመሩበት ቀን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ዕለቱ" የምክር ቀን" በመባል ይጠራል፡፡" መልካም መዓዛ ያለው" እና "የእንባ"ቀንም ይባላል። ምክንያቱም ማርያም ዕንተ እፍረት ዋጋው ብዙ የሆነ ሽቶ ጌታችንን በመቀባታና ስለ ሀጥያቷ ስቅስቅ ብላ በማልቀሷ ይህንን ስያሜ ተሰጠ። ማቴ 26፦3_13 ማር 14፦ 1_11 ሉቃ 22፦3_6
#ዕለተ_ሐሙስ/ሐሙስ/
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዕለት ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ለመግለጥ እና ለአርአያነት ጸሐፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ጸሎተ ሐሙስ በመባል ይታወቃል፡፡ ትሕትና ፍቅር መታዘዝ እንዲሁም የአገልግሎትን ትርጉም ለማስረዳትና ለማስገንዘብ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ሕጽበተ ሐሙስ በመባልም እንደሚጠራ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም «ወሶበ ኀፀቦሙ እገሪሆሙ ነሥአ አልባሲሁ ወረፈቀ ካዕበ ወይቤሎሙ አእመርክሙኑ ዘገበርኩ ለክሙ ... ወሶበ አነ እንከ ሊቅክሙ ወእግዚእክሙ ኀፀብኩክሙ እገሪክሙ ከማሁኬ አንትሙኒ ይደልወክሙ ትኅፅቡ እግረ ቢጽክሙ፡፡»፤ «እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ እንዲህም አላቸው ያደረግሁላችሁን ታስተውሉታላችሁን?... እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ እናንተ ደግሞ እርስ በእርሳችሁ ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል ሲል ተናግሯል፡፡ /ዮሐ.13-12-20/፡፡
ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚፈስ ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ በማለት ምሥጢረ ቁርባንን የመሠረተበት ወይም ራሱ ምስጢረ ቁርባንን የጀመረበት ቀን በመሆኑ የምስጢር ቀን ተብሎ ይጠራል፡፡ ይኸውም የሰው ልጆች ሥጋውንና ደሙን ተቀብለን ከእርሱ ጋር አንድነትና ኅብረት እንዲኖረን ጥንተ ጠላት ዲለብሎስንም ፍጹም ድል ነሥተን ሰማያዊት ርስት መንግሥተ ሰማያትን እንድንወርስ ለማስቻል ነው፡፡ /ማቴ.26-26-29/፡፡
አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ በእነርሱ ጥበብና ፍላጐት ቀስ ብለው መጥተው የያዙበት ቀን ስለሆነ በዚህ ዕለት በለሆሳስ /ብዙ የድምጽ ጩኸት ሳይሰማ/ የቅዳሴ ሥርዓት ይፈጸማል፡፡ ስለሆነም መላው ሕዝበ ክርስቲያን በዚህ የሕጽበት፣ የምስጢር፣ የጸሎት ቀን በተባለው በዚህ ዕለት በንስሓ ታጥበው ሥጋ ወደሙ እንዲቀበሉ ቤተ ክርስቲያን በአጽንኦት ታስተምራለች፡፡
#ዕለተ_ዐርብ/ዓርብ/
ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ «አውቀውስ ቢሆን የክብርን ጌታ ባልሰቀሉት» /1ቆሮ.1-18/፡፡ እንዳለ ይህ ዕለት የአይሁድ ካህናት ያለበደል ያለጥፋት ንጹሕና ጻድቅ የሆነውን ጌታ የሰቀሉበት ዕለት ነው፡፡ ዕለቱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ መድኃኒት ለአዳምና ለልጆቹ ሲል በመልእልተ መስቀል በቀራንዮ አደባባይ ተሰቅሎ መዋሉን የምናስብበት ታላቅ ቀን ነው፡፡ /ማቴ.27-35-75/፡፡ በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ፡፡ እነርሱ ግን እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ፡፡ ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሔደና ታንቆ ሞተ፡፡ የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ፡፡ ተማክረውም የሸክላ ሠሪ መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት፡፡ ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ፡፡ /ማቴ.27-3-9/
የሰው ልጆች በዘር ኃጢአት /ቁራኝነት/ ይኖሩበት የነበረው የጨለማ ሕይወት ያከተመበት ፍጹም ድኅነት ያገኙባት ታላቅ ዕለት ናት፡፡ ክርስቲያኖች ሁልጊዜም ዕለተ ዓርብ ሲመጣ ሕማሙን ስቅለቱን ሞቱን የሚያስቡበት ጊዜ ነው፡፡ በሮማውያን ሕግና ሥርዓት መስቀል የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት የሕይወት መቅጫ አርማ ሆኖ ሳለ ለእኛ የዲያብሎስ ድል መንሻ ስላደረገው በስቅለቱና በሞቱም ሕይወትን ስለአገኘን በዚህም ምክንያት መልካሙ ዓርብ በመባል እንደሚታወቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ያትታሉ፡፡
በመስቀል ላይ ሳለ 7 ነገሮችን ተናገረ/7ቱ " አጽርሐ መስቀል " በመባል ይታወቃሉ። እነሱም፦
" አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ" ማቴ 17፦46
" አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" ሉቃ 23፦34
" ዛሬ በገነት ከኔ ጋር እንድትኖር በእውነት እነግርሀለሁ" ሉቃ 23፦4
" አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ" ሉቃ 23፦ 46
" እነሆ ልጅሽ እነኋት እናትህ" ዮሐ 19፦26
" ተጠማሁ" ዮሐ 19፦28
" ሁሉ ተፈጸመ " ዮሐ 19፦ 30
ጌታ ሁሉ ተፈጸመ ብሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ስጋው በራሱፈቃድ ከለየ በኋላ አምላክነቱን ለመግለፅ የታዩ ተአምራት የሚከተሉት ናቸው፤
በሰማይ፤ /ማቴ 24፦29 እና 27፦45/
1. ፀሐይ ጨለመች
2. ጨረቃ ደም ሆነች
3. ከዋክብት ረገፉ
በምድር፤/ማቴ 27፦51_53/
1. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይእስከ ታች ተቀደደ
2. ምድር ተናወጠች
3. መቃብሮች ተከፈቱ
4. ሙታን ተነሱ
#ቀዳሜ_ስዑር/ቅዳሜ/
ዕለተ ቅዳሜ እግዚአብሔር የሚታዩትንና የማይታዩትን፣ በእግር የሚሄዱትን እና በክንፍ የሚበሩትን በባሕር የሚዋኙትን እንስሳትን በመጨረሻም ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ያረፈበት ዕለት ነች፡፡ ይህች የመጀመሪያው ቅዳሜ ለእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት ናት እግዚአብሔርን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ ስላረፈበት ሰንበት ዐባይ /ታላቋ ሰንበት/ ትባላለች ታላቋን ሰንበት እስራኤላውያን እንዲያከብሯት ታዟል፡፡ ዘፍ.1፡3፡፡
#ዕለተ_ቀዳሚት /ሰንበት ዐባይ/ በዘመነ ሐዲስም የተለየ የደኅነት ሥራ ተከናውኖባታል፡፡ ጥንት ሥነ ፈጥረትን በመፍጠር ዕረፍት እንደ ተደረገባት ሁሉ የፍጥረት ሁሉ ቁንጮ የሆነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው ቸሩ አምላክ በመቃብር አርፎባታል፡፡ ማቴ.27፡61፡፡
በዚህች ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ዐርፎ የዋለባት ዕለት በመሆኗ «ቀዳሜ ስዑር » ትሰኛለች፡፡ ስዑር ቀዳሜ የተባለችው በዓመት አንድ ቀን ስለ ምትጾም ነው፡፡ ምክንያቱም እናቱ ድንግል ማርያም ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት አንስተው ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደረጉት የነበረ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብ ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
ከቅዱሳን ሐዋርያት ሲወርድ ሲወራረድ በመጣው ትውፊት መሠረት ቅዱሳን ሐዋርያት በማዘን በመጾምና በመጸለይ ዕለቷ እንዳከበሯት የተዋሕዶ ልጆች የተቻላቸው ከዓርብ ጀምረው የሚያከፍሉ /የሚጾሙ/ ለሁለት ቀን እህል ውኃ ሳይቀምሱ ያድራሉ ያልተቻላቸው ደግሞ ዓርብ ማታ በልተው ቅዳሜን በመጾም ትንሣኤን ያከብራሉ፡፡
በዚህ ዕለት ከሰኞ ከሆሣዕና ማግሥት ጀምረው እስከ ስቅለተ ዓርብ ድረስ በስግደት እና በጾም ያሳለፉ ምእመናን በዕለተ ቅዳሜ በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን ይሰበሰባሉ፡፡ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ «ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፡-በመስቀሉ ሰላምን መሠረተ» የምሥራች እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡት ምእመናን ቄጠማ ይታደላል ቄጠማው የምሥራች ምልክት ነው፡፡ ቄጠማው የምሥራች ምልክት ተደርጐ የተወሰደው በኖህ ዘመን ከተፈጸመው ታሪክ ጋር በማቆራኘት ነው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሕዝቦች ከሕገ እግዚአብሔር ውጪ ሆነው እጅግ የሚያሳዝን ኃጢአት በሠሩ ጊዜ በንፍር ውኃ ተጥለቅልቀዋል፡፡ በወቅቱ ጻድቁ ኖኅ ወደ መርከብ ይዞአቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ይለቃታል፤ እርሷም ቄጠማ በአፍዋ ይዛ ትመልሳለች፡፡ ዘፍ.9-1-29፡፡ ኖኅም በዚህ ቄጠማ የውኃውን መድረቅ ተረድቶ ተደስቷል፡፡
« #ቄጠማ»፣ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች መንገሪያ እንደሆነ አሁንም በክርስቶስ ሞት ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ ስትል ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡ ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የሆነውን ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፡፡
የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሚያቃጥለው ዋዕየ ሲኦል /የሲኦል ቃጠሎ/ ወደ ልምላሜ ገነት ጥንተ ማኅደራቸው መመለሳቸውን በዚህ አኳሃን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
#ሃይማኖታዊና_ትውፊታዊ_ክንዋኔዎች_በሰሙነ_ሕማማት
በዐቢይ ጾም ከሠርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላሉ፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በእነዚህ ዕለታት ውስጥ የተለያዩ ትውፊታዊ እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች አሉ፡፡ ከነዚህ ክንዋኔዎች ውስጥ አለ መሳሳም፣ አክፍሎት፣ ቄጤማ ማሰር፣ ጥብጣብ፣ ጉልባን እና ሕጽበተ እግር ይገኙበታል፡፡ ስለእነዚህ ክንዋኔዎች በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስላለው ትውፊታዊ አፈጻጸም መዛግብት አገላብጠን እና በኢትዮጵያ ኣርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑትን ሊቀ ካህሃት ክንፈ ገብርኤል አልታዬን አነጋግረን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡
#አለመሳሳም
በሰሙነ ሕማማት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች መስቀል እንደማይሳለሙት ሁሉ መጨባበጥ፣ መሳሳምና የትከሻ ሰላምታ መለዋወጠን አይፈጽሙም፡፡ ሰላምታ የማንለዋወጥበት ምክንያት፣ አይሁድ ጌታን ለመስቀል ሰኞ እና ማክሰኞ መከሩ አልሠመረላቸውም፡፡ ምክራቸው የተፈጸመው ረቡዕ ነው፡፡
ስለዚህ አይሁድ አያንሾካሾኩ “እንስቀለው… አንግደለው” ብለው ይማከሩ ነበር፡፡ ያነን ለማስታወስ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡ መስቀልም አንሳለምም፡፡ ሳምንቱ የክፋት ምክር የተመከረበት እንጂ የፍቅርና የደስታ ሰላምታ የታየበት ባለመሆኑ ይህንን በማሰብ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡
ይሁዳ ጌታን በጠላቶቹ ለማስያዝ “እኔ የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት” ብሎ በሰላምታው ምልክት ሰጣቸው ይህ ሰላምታ አምሐ ቅድሳት አይደለም፤ ተንኮል የተሞላበት እንጂ፡፡ የዲያቢሎስም ሰላምታ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሔዋንን “ሰላም ለኪ” ብሎ ነው ያታለላት፣ የዲያቢሎስ እና የይሁዳ ሰላምታ ሰይጣናዊ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ወቅትና ሁኔታ ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ሰላምታ ልውውጥ የለም፡፡ ዛሬ እየተስተዋለ ያለው ይኸው ሰላምታ ያለመለዋወጥ ሁኔታ ሥርወ መሠረቱ ይህ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ እዚህ ትውልድ ላይ ደርሷል ይቀጥላልም፡፡
#ሕጽበተ_እግር
ጌታ በፍጹም ትሕትና የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት፣ ከሐዋርያት ጋር ግብር የገባበትና የክርስትና ሕይወት ማሕተም የሆነውን ምሥጢረ ቁርባን ያከናወነበት ዕለት ነው ጸሎተ ሐሙስ፡፡
ሕጽበተ እግር ጌታችን በዚህ ዕለት “አናንተ ለወንድማችሁ አንዲህ አድርጉ” ለማለት የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ምክንያት የተሰጠ ምሳሌ ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው “አኔ ለአናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም፣ መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም፤ ይህን ብታውቁ ብታደርጉትም ብፁዓን ናቸሁ” /ዮሐ.13÷16-17/ በማለት ትሕትናውን አሳይቷል፡፡
ጌታ በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር ሲያጥብ “እኔ መምህራችሁ ስሆን እግራችሁን ካጠብኳችሁ አርአያዬን ሰጥቻችኋለሁ፤ እናንተም የወንድማችሁን እግር ታጥቡ ዘንድ ይገባል፡፡ ነገር ግን ከእናንተ አንዱ ለሞት አሳልፎ ይሰጠኛል” አለ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም “ማን ይሆን?” አሉ፡፡ ጌታም “ኅብስት ቆርሼ፣ ከወጡ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ደነገጡ፡፡ ይሁዳን ማመልከቱ ደነገጡ፡፡ ይሁደን ማመልከቱ ነበር፤ ለጊዜው አልገባቸውም፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን የሐዋርያቱን እግር በማጠብ ትሕትናን ካስተማራቸው በኋላ፤ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሰጣቸው፤ የኦሪትን መሥዋዕት የሻረው እና መሥዋዕተ ሐዲስን የሠራው በዚሁ ዕለት ነው፡፡
በዚህ ሃይማኖታዊ መነሻነትም በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ድርጊቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ፡- በወሎና በጎንደር ከጉልባን በተጨማሪ በተለይ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት ብቻ የሚጋገር የተለየ ዳቦ አለ፡፡ ይህ ልዩ ዳቦ በወሎ “ትኩሴ” በጎንደር ደግሞ “ሙጌራ” ይባላል፡፡ ይህ ዳቦ ጌታ ለሐዋርያት የሰጣቸው ኅብስት አምሳያ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ ከዚህ ቀን ውጪ በሌላ ጊዜ አይጋገርም፡፡ በመሆኑም ሰው ሁሉ ዳቦውን ለመብላት የሚጠባበቀው በታላቅ ጉጉት ነው፡፡ አልፎ አልፎ ግን ሃይማኖታዊ ሥርዓት በሚከበርባቸው እንደ ማኅበርና ሰንበቴ በመሳሰሉት መንፈሳዊና ማኅበራዊ ትውፊቶች የሚቀርብበት ጊዜ አለ፡፡
በትግራይ በዕለተ ስቅለት ከተለመደው የጾምና የስግደት ሥርዓት በተጨማሪ የሚከናወኑ ድርጊቶች አሉ፡፡ በዕለቱ ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት መታሰቢያ ሲባል ወንዶች ልጆች በሙሉ ፀጉራቸውን እንዲላጩ ይደረጋል፡፡ ያን ቀን ያልተላጨ ልጅ “ኃጢአት ይሆንበታል” ስለሚባል ሳይላጭ የሚውል ልጅ የለም። ልጃገረዶች በበኩላቸው በዛፍ ላይ ገመድ በማሰር ዥዋዥዌ ይጫወታሉ፡፡ ይህንንም የሚያደርጉት የጌታን እንግልትና መስቀል ለማዘከር ነው ይባላል፡፡
እነሆ ይህንን ዕለት በማስታወስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ ቤተ ክርስቲያን ከሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ እስከ ቀሳውስት ያሉት አባቶች በያሉበት አጥቢያ /ደብር/ በመገኘት በመዓርግ የሚያንሷቸውን የካህናት፣ ዲያቆናት እና የምእመናንን እግር ያጥባሉ፤ የሚያጥቡትም የወይራ እና የወይን ቅጠል በመዘፍዘፍ ነው፡፡
#አክፍሎት
በሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ ከስግደት በኋላ ምእመናን በየቤታቸው ጥቂት ነገር ለቁመተ ሥጋ ቀምሰው እስከ እሑድ /የትንሣኤ ሰዓት/ ይሰነብታሉ፡፡ ይህ አክፍሎት ይባላል፡፡ ብዙው ምዕመን ከዓርብ ጀምሮ የሚያከፍል ሲሆን አንዳንዶች ግን ከሐሙስ ጀምረው ያከፍላሉ፡፡ ይህም እመቤታችን፣ ያዕቆብ እና ዮሐንስ የጌታን ትንሣኤ ሳናይ እህል ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሣኤ መቆየታቸውን ተከትሎ የመጣ ትውፊት ነው፡፡
ይህንን ትውፊት አስመልክቶ ሄሬኔዎስ፣ አውሳብዮስ የተባሉ ጸሐፍት፤ ሐዋርያት በሰሙነ ሕማማት ከደረቅ ዳቦ አና ከትንሽ ውኃ በቀር እንደማይመገቡ እና ከሐሙስ ጀምረው እንደሚያከፍሉ ጽፈዋል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ሐዋርያት ሌሎቹንም እንዲያከፍሉ እንዳሳሰቡና ከሐሙስ ጀምሮ ያልተቻለው ቢያንስ ከዓርብ ጀምሮ እንዲያከፍል ማዘዛቸውን ጽፈዋል፡፡ የእኛ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትም ይኸው ነው፡፡ ቅዳሜ ይበላል ማለት ግን ቅዳሴው ሌሊት ስለሆነ በልቶ ማስቀደስ ነውና በልቶ እንደመቁረብ ይቆጠራል፡፡
#ጉልባን_እና_ቄጤማ
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚባላ ንፍሮ ነው፡፡ የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር፤ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበር፡፡ ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታሰባል፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ይህንን መሠረት በማድረግ የሚዘጋጀው ጉልባን አንዲህም ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ጨው ውኃ የሚያስጠማ በመሆኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሥርዓት ከእስራኤላውያን የመጣ ሲሆን በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ሥርዓቱ ዛሬም ይከበራል፡፡
#ጥብጣብ
በሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ የስቅለቱ መታሰቢያ ነው፡፡ ምእመናኑ በሰሙነ ሕማማት የሠሩትን ይናዘዛሉ፡፡ ካህናቱም በወይራ ቅጠል ትከሻቸወን እየጠበጠቡ ቀን ከሰገዱት ስግደት በተጨማሪ ሌላ ስግደት ያዟቸዋል፡፡ ጥብጠባው የተግሳፅ ምሳሌ ነው፡፡ ጥብጣብ የሚደረግለት ሰው በሕማማቱ ወቅት የፈጸመው በደል ወይንም ኃጢአት ካለ ይህንኑ በመናገር የስግደቱ ቁጥር ከፍ እንዲል ይደረጋል፡፡
ይህ በስቅለት ቀን የሚፈጸም ሥነ ሥርዓት ሲሆን፤ ጠብጣቤ ማለት ቸብ ቸብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዕለተ ስቅለት ሲሰግድ ሲጸልይ፣ ሲያነብ ከዋለ በኋላ ሰርሆተ ሕዝብ /የሕዝብ መሰነባበቻ/ ከመሆኑ በፊት፤ በወይራ ቅጠል እያንዳንዱን ምእመን ጀርባ ቸብ ቸብ መደረጉ፣ የጌታን ግርፋት ያስታውሳል፡፡
#ቀጤማ
በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለ ዓዋዲ/ እየመቱ “ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ” የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቀጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቀጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ የደፉበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቀጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጭሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
ያብጽሃነ ያብጽሕክሙ!
(ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ ሕማማት
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀል በችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።
በዚህ ሳምንት ውስጥ ካህናትና ምዕመናን በአፀደ ቤተ ክርስትያን ተሰብስበው ከሀጥያት ርቀው ከምግብና ከመጠጥ ተቆጥቦ በጾምና በጸሎት የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ ሲያዜሙ ግብረ ሕማም የሚባለውን መጽሐፍ እያነበቡ ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ።
ከአባታችን አዳም በደል ወይንም ስሕተት በኋላ በሕማማት፣ በደዌያት፣ በመቅሰፍታት፣ ወዘተ በብዙ መከራ የሰው ልጅ ሊኖርባቸው ግድ የሆነባቸው ዘመናት ጥቂቶች አልነበሩም፡፡ ጥሮ ግሮ ወጥቶ ወርዶ ለፍቶ ማስኖ የዕለት ጉርስ የቀን ልብስ ማግኘት እጅግ አዳጋች ነበር፡፡ ሁልጊዜ የሰው ልጅ ቢያጠፋ ቢበድል ከሕገ እግዚአብሔር ቢወጣ እንኳ የዋህ፣ ታጋሽ፣ ቸር፣ አዛኝ የሆነ አምላክ የጠፋውን ሊፈለግ የተራበውን ሊያጠግብ የታረዘውን ሊያለብስ፣ ፍቅር ያጣውን ፍጹም ፍቅር ሊለግስ፣ ሰላም ለሌለው ፍጹም ሰላም ሊሰጥ፣ ተስፋ የሌለውን ተስፋ ሊያጐናጽፍ ከሰማይ ወረደ፤ ከድንግል ማርያም ተወለደ፤ በገዳመ ቆሮንቶስ አርባ ቀንና ሌሊት ጾመ፡፡ በጾሙም የኃጡአት ሥሮች ወይም ራሶች የተባሉትን ስስትን፣ ትዕቢትንና ፍቅረ ንዋይን ድል አደረገልን፡፡ እኛ እርሱ የጾመውን ጾም እንድናከብር እንድንጾም ምሳሌ ሆነን፡፡ ዲያብሎስን ድል አድርጐ ድል እንድንነሣው ኃይልና ምሳሌ ሆነን፡፡
#ሰሙነ_ሕማማት_ምንድን_ነው?
ሰመነ ስምንት /ሳምንት/ አደረገ ማለት ነው፡፡ ይኸውም ከዕለተ ሆሣዕና ሰርክ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ያለውን ጊዜ ወይም ቀናት የሚያመለክት ነው፡፡ ሐመ ማለት ታመመ ማለት ሲሆን ይህም የሰውን ዘር ሁሉ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ ለማውጣት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ የተቀበላቸውን ጸዋትወ መከራዎች የሚያሳስብ ነው፡፡ ዕለታቱ የዓመተ ኩነኔ ወይም የዓመተ ፍዳ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት፣ የሚያለቅሱበት፣ የሚሰግዱበት ቤት ንብረታቸውን ትተው ከሌላው ቀናትና ጊዜያት በተለየ መልኩ ቤተ ክርስቲያናቸውን የሚማጸኑበት፤ ጧት ማታ ደጅ የሚጠኑበት፤ ኃጢአታቸውን በቤተ ክርስቲያን አደባባይ ለካህኑ የሚናዘዙበት በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ የሚገኝ ሳምንት ነው፡፡
በዚህ ሳምንት ብዙ አዝማደ መባልእት አይበሉም፤ ይልቁን በመራብ በመጠማት በመውጣት በመውረድ በመስገድ በመጸለይ በመጾም በየሰዓቱ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጸዋትወ መከራዎች በማሰብ አብዝቶ ይሰገዳል፡፡ መከራውን፣ ሕማሙን፣ ድካሙን የሚያስታውሱ ከቅዱሳት መጻሕፍት ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ መዝሙረ ዳዊት ግብረ ሕማማት ወዘተ በየሰዓቱ ይነበባል፡፡
#መስቀል_መሳለም_የለም፡፡ ካህናትም እግዚአብሔር ይፍታህ አይሉም የሳምንቱ ሥርዓተ ፍትሐት አይደረግም፡፡ ይኸውም ይህ ሳምንት ከሞት ወደ ሕይወት የተሸጋገርንበት ከጨለማ ወደ ብርሃን የተጓዝንበት የመሸጋገሪያ ወቅት ምሳሌ በመሆኑ ነው፡፡ በዕለተ ምጽአት መላእክት የመለከት ድምጽ በማሰማት የዳግም ምጽአትን ዕለት ለማሳሰብ ምእመናን ጥሪውን ሰምተው ለዚህም አስቀድመው ተዘጋጅተው የበዓሉ ታዳሚዎች መሆናቸውን በማጠየቅ በዚህ ሳምንት ዲያቆኑ ቃጭል እየመታ በየሰዓቱ ምእመናኑን ያሳስባል፡፡
#በሰሙነ_ሕማማት_የሚገኙ_ዕለታትና_ስያሜያት
#ዕለተ_ሰኑይ /ሰኞ/
ይህ ዕለት አንጾሖተ ቤተ መቅደስ /የቤተ መቅደስ መንጻት/ እና መርገመ በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው፡፡ /ማር.11-11፣ ማቴ.21-18-22 ሉቃ.13-6-9/፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ «ወመሰለ ሎሙ ወይቤሎሙ አሐዱ ብእሲ በለሰ ቦቱ ውስተ አጸደ ወይኑ ወየሐውር ይንሣእ ፍሬሃ ወኢይረክብ ...»፤ ይህንም ምሳሌ አለ ለአንድ ሰው በወይኑ አትክልት የተተከለች በለስ ነበረችው ፍሬም ሊፈልግባት ወጥቶ ምንም አላገኘም፡፡ በማለት በበለስ ስለተመሰለ የሰው ልጅ ሕይወት በማሰብ እንዲመለስ ንስሐ እንዲገባ በሕይወትም እንዲኖር እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ማሳሰቡን ያጠይቃል፡፡ ንስሐ አልገባም አልመለስም ያለም በለሷ እንደጠወለገችና እንደተቆረጠች ሁሉ ፍሬ ባለማፍራታቸው እንደሚቆረጡ እንዲሁም ወደ እሳት እንደሚጣሉ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ፍሬ የተባለ ደግሞ ሃይማኖትና ምግባርን ነው፡፡ ሁላችን ቤተ እስራኤላውያን ፍሬ ሃይማኖት ወምግባር አስተባብረን ይዘን መገኘት ይገባናል፡፡ ፍሬ አልባ እንዳንሆን ጌታ ሲመጣም እንዳናፍር የመጽሐፉን ቃል ልንጠብቅና ልንፈጽም ይገባናል፡፡ በዚህ የሕማማት የመጀመሪያ ቀን ዕለተ ሰኑይ የምናስበው የምንዘክረው የሰው ልጅ ሕይወት በከንቱ በቸልተኝነት እንዳይደክም እንዳይጠወለግ እንዳይደርቅ ወደ እሳትም እንዳይጣል ማድረግ ይገባናል፡፡
#ዕለተ_ሠሉስ /ማክሰኞ/
ይህ ቀን ጌታችን ሰኞ በተናገረውና ባደረገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀረቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማረበት ዕለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የጥያቄ እና የትምህርት ቀን በመባል ይታወቃል፡፡ ጥያቄውም ጌታ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት ለጸሐፍትና ፈሪሳውያን ይኸውም ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታትን በማን ሥልጣን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ?» የሚል ነበር፡፡ /ማቴ.21-23-27/፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ «ወይቤሎሙ ኢየሱስ አማን እብለክሙ ከመ መጸብሓውያን ወዘማውያት ይቀድሙክሙ ውስተ መንግሥተ እግዚአብሔር»፤ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው እውነት እላችኋለሁ ቀራጮችና ጋለሞቶች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በመግባት ይቀድሙአችኋል ሲል አስተምሯል፡፡ /ማቴ.21-28/
#ዕለተ_ረቡዕ/እሮብ/
ይህ ዕለት ደግሞ የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚችሉ ምክር የጀመሩበት ቀን ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ዕለቱ" የምክር ቀን" በመባል ይጠራል፡፡" መልካም መዓዛ ያለው" እና "የእንባ"ቀንም ይባላል። ምክንያቱም ማርያም ዕንተ እፍረት ዋጋው ብዙ የሆነ ሽቶ ጌታችንን በመቀባታና ስለ ሀጥያቷ ስቅስቅ ብላ በማልቀሷ ይህንን ስያሜ ተሰጠ። ማቴ 26፦3_13 ማር 14፦ 1_11 ሉቃ 22፦3_6
#ዕለተ_ሐሙስ/ሐሙስ/
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዕለት ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ለመግለጥ እና ለአርአያነት ጸሐፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ጸሎተ ሐሙስ በመባል ይታወቃል፡፡ ትሕትና ፍቅር መታዘዝ እንዲሁም የአገልግሎትን ትርጉም ለማስረዳትና ለማስገንዘብ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ሕጽበተ ሐሙስ በመባልም እንደሚጠራ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም «ወሶበ ኀፀቦሙ እገሪሆሙ ነሥአ አልባሲሁ ወረፈቀ ካዕበ ወይቤሎሙ አእመርክሙኑ ዘገበርኩ ለክሙ ... ወሶበ አነ እንከ ሊቅክሙ ወእግዚእክሙ ኀፀብኩክሙ እገሪክሙ ከማሁኬ አንትሙኒ ይደልወክሙ ትኅፅቡ እግረ ቢጽክሙ፡፡»፤ «እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ እንዲህም አላቸው ያደረግሁላችሁን ታስተውሉታላችሁን?... እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ እናንተ ደግሞ እርስ በእርሳችሁ ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል ሲል ተናግሯል፡፡ /ዮሐ.13-12-20/፡፡
ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚፈስ ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ በማለት ምሥጢረ ቁርባንን የመሠረተበት ወይም ራሱ ምስጢረ ቁርባንን የጀመረበት ቀን በመሆኑ የምስጢር ቀን ተብሎ ይጠራል፡፡ ይኸውም የሰው ልጆች ሥጋውንና ደሙን ተቀብለን ከእርሱ ጋር አንድነትና ኅብረት እንዲኖረን ጥንተ ጠላት ዲለብሎስንም ፍጹም ድል ነሥተን ሰማያዊት ርስት መንግሥተ ሰማያትን እንድንወርስ ለማስቻል ነው፡፡ /ማቴ.26-26-29/፡፡
አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ በእነርሱ ጥበብና ፍላጐት ቀስ ብለው መጥተው የያዙበት ቀን ስለሆነ በዚህ ዕለት በለሆሳስ /ብዙ የድምጽ ጩኸት ሳይሰማ/ የቅዳሴ ሥርዓት ይፈጸማል፡፡ ስለሆነም መላው ሕዝበ ክርስቲያን በዚህ የሕጽበት፣ የምስጢር፣ የጸሎት ቀን በተባለው በዚህ ዕለት በንስሓ ታጥበው ሥጋ ወደሙ እንዲቀበሉ ቤተ ክርስቲያን በአጽንኦት ታስተምራለች፡፡
#ዕለተ_ዐርብ/ዓርብ/
ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ «አውቀውስ ቢሆን የክብርን ጌታ ባልሰቀሉት» /1ቆሮ.1-18/፡፡ እንዳለ ይህ ዕለት የአይሁድ ካህናት ያለበደል ያለጥፋት ንጹሕና ጻድቅ የሆነውን ጌታ የሰቀሉበት ዕለት ነው፡፡ ዕለቱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ መድኃኒት ለአዳምና ለልጆቹ ሲል በመልእልተ መስቀል በቀራንዮ አደባባይ ተሰቅሎ መዋሉን የምናስብበት ታላቅ ቀን ነው፡፡ /ማቴ.27-35-75/፡፡ በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ፡፡ እነርሱ ግን እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ፡፡ ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሔደና ታንቆ ሞተ፡፡ የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ፡፡ ተማክረውም የሸክላ ሠሪ መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት፡፡ ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ፡፡ /ማቴ.27-3-9/
የሰው ልጆች በዘር ኃጢአት /ቁራኝነት/ ይኖሩበት የነበረው የጨለማ ሕይወት ያከተመበት ፍጹም ድኅነት ያገኙባት ታላቅ ዕለት ናት፡፡ ክርስቲያኖች ሁልጊዜም ዕለተ ዓርብ ሲመጣ ሕማሙን ስቅለቱን ሞቱን የሚያስቡበት ጊዜ ነው፡፡ በሮማውያን ሕግና ሥርዓት መስቀል የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት የሕይወት መቅጫ አርማ ሆኖ ሳለ ለእኛ የዲያብሎስ ድል መንሻ ስላደረገው በስቅለቱና በሞቱም ሕይወትን ስለአገኘን በዚህም ምክንያት መልካሙ ዓርብ በመባል እንደሚታወቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ያትታሉ፡፡
በመስቀል ላይ ሳለ 7 ነገሮችን ተናገረ/7ቱ " አጽርሐ መስቀል " በመባል ይታወቃሉ። እነሱም፦
" አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ" ማቴ 17፦46
" አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው" ሉቃ 23፦34
" ዛሬ በገነት ከኔ ጋር እንድትኖር በእውነት እነግርሀለሁ" ሉቃ 23፦4
" አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ" ሉቃ 23፦ 46
" እነሆ ልጅሽ እነኋት እናትህ" ዮሐ 19፦26
" ተጠማሁ" ዮሐ 19፦28
" ሁሉ ተፈጸመ " ዮሐ 19፦ 30
ጌታ ሁሉ ተፈጸመ ብሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ስጋው በራሱፈቃድ ከለየ በኋላ አምላክነቱን ለመግለፅ የታዩ ተአምራት የሚከተሉት ናቸው፤
በሰማይ፤ /ማቴ 24፦29 እና 27፦45/
1. ፀሐይ ጨለመች
2. ጨረቃ ደም ሆነች
3. ከዋክብት ረገፉ
በምድር፤/ማቴ 27፦51_53/
1. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይእስከ ታች ተቀደደ
2. ምድር ተናወጠች
3. መቃብሮች ተከፈቱ
4. ሙታን ተነሱ
#ቀዳሜ_ስዑር/ቅዳሜ/
ዕለተ ቅዳሜ እግዚአብሔር የሚታዩትንና የማይታዩትን፣ በእግር የሚሄዱትን እና በክንፍ የሚበሩትን በባሕር የሚዋኙትን እንስሳትን በመጨረሻም ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ያረፈበት ዕለት ነች፡፡ ይህች የመጀመሪያው ቅዳሜ ለእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት ናት እግዚአብሔርን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ ስላረፈበት ሰንበት ዐባይ /ታላቋ ሰንበት/ ትባላለች ታላቋን ሰንበት እስራኤላውያን እንዲያከብሯት ታዟል፡፡ ዘፍ.1፡3፡፡
#ዕለተ_ቀዳሚት /ሰንበት ዐባይ/ በዘመነ ሐዲስም የተለየ የደኅነት ሥራ ተከናውኖባታል፡፡ ጥንት ሥነ ፈጥረትን በመፍጠር ዕረፍት እንደ ተደረገባት ሁሉ የፍጥረት ሁሉ ቁንጮ የሆነውን አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው ቸሩ አምላክ በመቃብር አርፎባታል፡፡ ማቴ.27፡61፡፡
በዚህች ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ዐርፎ የዋለባት ዕለት በመሆኗ «ቀዳሜ ስዑር » ትሰኛለች፡፡ ስዑር ቀዳሜ የተባለችው በዓመት አንድ ቀን ስለ ምትጾም ነው፡፡ ምክንያቱም እናቱ ድንግል ማርያም ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት አንስተው ብርሃነ ትንሣኤውን እስኪያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደረጉት የነበረ አምላካቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ሞቱን በማሰብ ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
ከቅዱሳን ሐዋርያት ሲወርድ ሲወራረድ በመጣው ትውፊት መሠረት ቅዱሳን ሐዋርያት በማዘን በመጾምና በመጸለይ ዕለቷ እንዳከበሯት የተዋሕዶ ልጆች የተቻላቸው ከዓርብ ጀምረው የሚያከፍሉ /የሚጾሙ/ ለሁለት ቀን እህል ውኃ ሳይቀምሱ ያድራሉ ያልተቻላቸው ደግሞ ዓርብ ማታ በልተው ቅዳሜን በመጾም ትንሣኤን ያከብራሉ፡፡
በዚህ ዕለት ከሰኞ ከሆሣዕና ማግሥት ጀምረው እስከ ስቅለተ ዓርብ ድረስ በስግደት እና በጾም ያሳለፉ ምእመናን በዕለተ ቅዳሜ በቅጽረ ቤተ ክርስቲያን ይሰበሰባሉ፡፡ የጠዋቱ ጸሎት ሲፈጸም ካህናቱ «ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፡-በመስቀሉ ሰላምን መሠረተ» የምሥራች እያሉ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡት ምእመናን ቄጠማ ይታደላል ቄጠማው የምሥራች ምልክት ነው፡፡ ቄጠማው የምሥራች ምልክት ተደርጐ የተወሰደው በኖህ ዘመን ከተፈጸመው ታሪክ ጋር በማቆራኘት ነው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሕዝቦች ከሕገ እግዚአብሔር ውጪ ሆነው እጅግ የሚያሳዝን ኃጢአት በሠሩ ጊዜ በንፍር ውኃ ተጥለቅልቀዋል፡፡ በወቅቱ ጻድቁ ኖኅ ወደ መርከብ ይዞአቸው ከገባው እንስሳት መካከል የውኃውን መጉደል ለመረዳት ርግብን በመርከብ መስኮት አሾልኮ ይለቃታል፤ እርሷም ቄጠማ በአፍዋ ይዛ ትመልሳለች፡፡ ዘፍ.9-1-29፡፡ ኖኅም በዚህ ቄጠማ የውኃውን መድረቅ ተረድቶ ተደስቷል፡፡
« #ቄጠማ»፣ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች መንገሪያ እንደሆነ አሁንም በክርስቶስ ሞት ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ ስትል ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡ ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የሆነውን ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፡፡
የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሚያቃጥለው ዋዕየ ሲኦል /የሲኦል ቃጠሎ/ ወደ ልምላሜ ገነት ጥንተ ማኅደራቸው መመለሳቸውን በዚህ አኳሃን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
#ሃይማኖታዊና_ትውፊታዊ_ክንዋኔዎች_በሰሙነ_ሕማማት
በዐቢይ ጾም ከሠርክ ሆሣዕና ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላሉ፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በእነዚህ ዕለታት ውስጥ የተለያዩ ትውፊታዊ እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች አሉ፡፡ ከነዚህ ክንዋኔዎች ውስጥ አለ መሳሳም፣ አክፍሎት፣ ቄጤማ ማሰር፣ ጥብጣብ፣ ጉልባን እና ሕጽበተ እግር ይገኙበታል፡፡ ስለእነዚህ ክንዋኔዎች በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስላለው ትውፊታዊ አፈጻጸም መዛግብት አገላብጠን እና በኢትዮጵያ ኣርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑትን ሊቀ ካህሃት ክንፈ ገብርኤል አልታዬን አነጋግረን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡
#አለመሳሳም
በሰሙነ ሕማማት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች መስቀል እንደማይሳለሙት ሁሉ መጨባበጥ፣ መሳሳምና የትከሻ ሰላምታ መለዋወጠን አይፈጽሙም፡፡ ሰላምታ የማንለዋወጥበት ምክንያት፣ አይሁድ ጌታን ለመስቀል ሰኞ እና ማክሰኞ መከሩ አልሠመረላቸውም፡፡ ምክራቸው የተፈጸመው ረቡዕ ነው፡፡
ስለዚህ አይሁድ አያንሾካሾኩ “እንስቀለው… አንግደለው” ብለው ይማከሩ ነበር፡፡ ያነን ለማስታወስ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡ መስቀልም አንሳለምም፡፡ ሳምንቱ የክፋት ምክር የተመከረበት እንጂ የፍቅርና የደስታ ሰላምታ የታየበት ባለመሆኑ ይህንን በማሰብ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡
ይሁዳ ጌታን በጠላቶቹ ለማስያዝ “እኔ የምስመው እርሱ ነው፤ ያዙት” ብሎ በሰላምታው ምልክት ሰጣቸው ይህ ሰላምታ አምሐ ቅድሳት አይደለም፤ ተንኮል የተሞላበት እንጂ፡፡ የዲያቢሎስም ሰላምታ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሔዋንን “ሰላም ለኪ” ብሎ ነው ያታለላት፣ የዲያቢሎስ እና የይሁዳ ሰላምታ ሰይጣናዊ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ወቅትና ሁኔታ ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ሰላምታ ልውውጥ የለም፡፡ ዛሬ እየተስተዋለ ያለው ይኸው ሰላምታ ያለመለዋወጥ ሁኔታ ሥርወ መሠረቱ ይህ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ እዚህ ትውልድ ላይ ደርሷል ይቀጥላልም፡፡
#ሕጽበተ_እግር
ጌታ በፍጹም ትሕትና የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት፣ ከሐዋርያት ጋር ግብር የገባበትና የክርስትና ሕይወት ማሕተም የሆነውን ምሥጢረ ቁርባን ያከናወነበት ዕለት ነው ጸሎተ ሐሙስ፡፡
ሕጽበተ እግር ጌታችን በዚህ ዕለት “አናንተ ለወንድማችሁ አንዲህ አድርጉ” ለማለት የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ምክንያት የተሰጠ ምሳሌ ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው “አኔ ለአናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም፣ መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም፤ ይህን ብታውቁ ብታደርጉትም ብፁዓን ናቸሁ” /ዮሐ.13÷16-17/ በማለት ትሕትናውን አሳይቷል፡፡
ጌታ በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር ሲያጥብ “እኔ መምህራችሁ ስሆን እግራችሁን ካጠብኳችሁ አርአያዬን ሰጥቻችኋለሁ፤ እናንተም የወንድማችሁን እግር ታጥቡ ዘንድ ይገባል፡፡ ነገር ግን ከእናንተ አንዱ ለሞት አሳልፎ ይሰጠኛል” አለ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም “ማን ይሆን?” አሉ፡፡ ጌታም “ኅብስት ቆርሼ፣ ከወጡ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ደነገጡ፡፡ ይሁዳን ማመልከቱ ደነገጡ፡፡ ይሁደን ማመልከቱ ነበር፤ ለጊዜው አልገባቸውም፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን የሐዋርያቱን እግር በማጠብ ትሕትናን ካስተማራቸው በኋላ፤ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሰጣቸው፤ የኦሪትን መሥዋዕት የሻረው እና መሥዋዕተ ሐዲስን የሠራው በዚሁ ዕለት ነው፡፡
በዚህ ሃይማኖታዊ መነሻነትም በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ድርጊቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ፡- በወሎና በጎንደር ከጉልባን በተጨማሪ በተለይ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት ብቻ የሚጋገር የተለየ ዳቦ አለ፡፡ ይህ ልዩ ዳቦ በወሎ “ትኩሴ” በጎንደር ደግሞ “ሙጌራ” ይባላል፡፡ ይህ ዳቦ ጌታ ለሐዋርያት የሰጣቸው ኅብስት አምሳያ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ ከዚህ ቀን ውጪ በሌላ ጊዜ አይጋገርም፡፡ በመሆኑም ሰው ሁሉ ዳቦውን ለመብላት የሚጠባበቀው በታላቅ ጉጉት ነው፡፡ አልፎ አልፎ ግን ሃይማኖታዊ ሥርዓት በሚከበርባቸው እንደ ማኅበርና ሰንበቴ በመሳሰሉት መንፈሳዊና ማኅበራዊ ትውፊቶች የሚቀርብበት ጊዜ አለ፡፡
በትግራይ በዕለተ ስቅለት ከተለመደው የጾምና የስግደት ሥርዓት በተጨማሪ የሚከናወኑ ድርጊቶች አሉ፡፡ በዕለቱ ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት መታሰቢያ ሲባል ወንዶች ልጆች በሙሉ ፀጉራቸውን እንዲላጩ ይደረጋል፡፡ ያን ቀን ያልተላጨ ልጅ “ኃጢአት ይሆንበታል” ስለሚባል ሳይላጭ የሚውል ልጅ የለም። ልጃገረዶች በበኩላቸው በዛፍ ላይ ገመድ በማሰር ዥዋዥዌ ይጫወታሉ፡፡ ይህንንም የሚያደርጉት የጌታን እንግልትና መስቀል ለማዘከር ነው ይባላል፡፡
እነሆ ይህንን ዕለት በማስታወስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሐዶ ቤተ ክርስቲያን ከሊቃነ ጳጳሳት ጀምሮ እስከ ቀሳውስት ያሉት አባቶች በያሉበት አጥቢያ /ደብር/ በመገኘት በመዓርግ የሚያንሷቸውን የካህናት፣ ዲያቆናት እና የምእመናንን እግር ያጥባሉ፤ የሚያጥቡትም የወይራ እና የወይን ቅጠል በመዘፍዘፍ ነው፡፡
#አክፍሎት
በሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ ከስግደት በኋላ ምእመናን በየቤታቸው ጥቂት ነገር ለቁመተ ሥጋ ቀምሰው እስከ እሑድ /የትንሣኤ ሰዓት/ ይሰነብታሉ፡፡ ይህ አክፍሎት ይባላል፡፡ ብዙው ምዕመን ከዓርብ ጀምሮ የሚያከፍል ሲሆን አንዳንዶች ግን ከሐሙስ ጀምረው ያከፍላሉ፡፡ ይህም እመቤታችን፣ ያዕቆብ እና ዮሐንስ የጌታን ትንሣኤ ሳናይ እህል ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሣኤ መቆየታቸውን ተከትሎ የመጣ ትውፊት ነው፡፡
ይህንን ትውፊት አስመልክቶ ሄሬኔዎስ፣ አውሳብዮስ የተባሉ ጸሐፍት፤ ሐዋርያት በሰሙነ ሕማማት ከደረቅ ዳቦ አና ከትንሽ ውኃ በቀር እንደማይመገቡ እና ከሐሙስ ጀምረው እንደሚያከፍሉ ጽፈዋል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ሐዋርያት ሌሎቹንም እንዲያከፍሉ እንዳሳሰቡና ከሐሙስ ጀምሮ ያልተቻለው ቢያንስ ከዓርብ ጀምሮ እንዲያከፍል ማዘዛቸውን ጽፈዋል፡፡ የእኛ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትም ይኸው ነው፡፡ ቅዳሜ ይበላል ማለት ግን ቅዳሴው ሌሊት ስለሆነ በልቶ ማስቀደስ ነውና በልቶ እንደመቁረብ ይቆጠራል፡፡
#ጉልባን_እና_ቄጤማ
ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚባላ ንፍሮ ነው፡፡ የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር፤ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበር፡፡ ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታሰባል፡፡
በጸሎተ ሐሙስ ይህንን መሠረት በማድረግ የሚዘጋጀው ጉልባን አንዲህም ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡ ጨው ውኃ የሚያስጠማ በመሆኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡ ይህ ትውፊታዊ ሥርዓት ከእስራኤላውያን የመጣ ሲሆን በኢትዮጵያም አብዛኛዎቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ሥርዓቱ ዛሬም ይከበራል፡፡
#ጥብጣብ
በሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ የስቅለቱ መታሰቢያ ነው፡፡ ምእመናኑ በሰሙነ ሕማማት የሠሩትን ይናዘዛሉ፡፡ ካህናቱም በወይራ ቅጠል ትከሻቸወን እየጠበጠቡ ቀን ከሰገዱት ስግደት በተጨማሪ ሌላ ስግደት ያዟቸዋል፡፡ ጥብጠባው የተግሳፅ ምሳሌ ነው፡፡ ጥብጣብ የሚደረግለት ሰው በሕማማቱ ወቅት የፈጸመው በደል ወይንም ኃጢአት ካለ ይህንኑ በመናገር የስግደቱ ቁጥር ከፍ እንዲል ይደረጋል፡፡
ይህ በስቅለት ቀን የሚፈጸም ሥነ ሥርዓት ሲሆን፤ ጠብጣቤ ማለት ቸብ ቸብ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዕለተ ስቅለት ሲሰግድ ሲጸልይ፣ ሲያነብ ከዋለ በኋላ ሰርሆተ ሕዝብ /የሕዝብ መሰነባበቻ/ ከመሆኑ በፊት፤ በወይራ ቅጠል እያንዳንዱን ምእመን ጀርባ ቸብ ቸብ መደረጉ፣ የጌታን ግርፋት ያስታውሳል፡፡
#ቀጤማ
በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለ ዓዋዲ/ እየመቱ “ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ” የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቀጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቀጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ የደፉበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቀጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጭሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
ያብጽሃነ ያብጽሕክሙ!
(ምንጭ፦ ስምዐ ጽድቅ ልዩ እትም ዘሰሙነ ሕማማት
Subscribe to:
Posts (Atom)