ዘወረደ |
በዲያቆን ስመኘው ጌትዬ
የካቲት 26 ቀን 2008 ዓ.ም.
እንኳን ለዓቢይ ጾም በሰላም አደረሰን። የ፳፻፰ (2008) ዓ.ም ዓቢይ ጾም የካቲት ፳፰(28) ቀንተጀምሮ ሚያዝያ ፳፫ (23) ቀን ይፈጸማል። ይህ ጾም በ 8 ታላላቅ ሳምንታት የተከፋፈለ ሲሆንእነርሱም ዘወረደ፣ ቅድስት፣ ምኲራብ፣ መጻጒዕ ፣ ደብረዘይት፣ ገብርኄር፣ ኒቆዲሞስ፣ እና ሆሳዕናይባላሉ፡፡ በዚህ ጾም ውስጥ በአጠቃላይ ጾመ እግዚእነ (የጌታችን ጾም) አርባውን ቀን ሲይዝየመጀመሪያው ሳምንት ጾመ ሕርቃል እና የመጨረሻው ሳምንት የጌታን ሕማማት የምናስብበትሰሙነ ሕማማት የቀረውን ክፍል ይይዛሉ፡፡
ዛሬ የመጀመሪያውን ሳምንት ወይም ዘወረደ የተባለውን ጾም ስያሜውን እና ምስጢሩን በታላቁሊቅ ቅዱስ ያሬድ ትምህርት እንዴት እንደተገለጠ እናያለን፡፡ የብሉያት እና የሐዲሳት መጽሐፍትሊቅ ቅዱስ ያሬድ ከጸዋትወ ዜማ መጽሐፍቱ አንዱ በሆነው የድጓ ክፍል ጾመ ድጓ (በጾምስለሚደረስ ጾመ ድጓ ተብሏል) ስለ ጾም ብዙ ጽፏል።ከዘወረደ ጀምሮ ያሉት ስምንቱም ሳምንታትስያሜያቸውን ያገኙት ከጾመ ድጓ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በተለይ ዋዜማክፍሉ ላይ ያሉትን የመጀመሪያ ቀለማት በመምረጥ የየሳምንታቱን ስያሜዎች አስገኝቷል፡፡ በዘወረደድርሰቱ ቅዱስ ያሬድ በጾም ልናስባቸው እና ልናከናውናቸው የሚገቡንን ነገሮች ከሥነምግባር፣ከጸሎት፣ ከቤተክርስቲያን፣ ከመስቀሉ አንፃር እየሆነ ይነግረናል፡፡ ዛሬ በዘወረደ ድርሰቱከተገለጡት በጥቂቱ እያነበብን እንማማራለን።
ቅዱስ ያሬድ የጾሙን ድርሰት ሲጀምር “ሃሌ ሉያ “ ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን አሳልፎ የሚኖርሁሉን የጀመረ ሁሉን የሚያስጀምር ሁሉን የፈጸመ ሁሉን የሚያስፈጽም ጾማችንንም እንዲሁያድርግልን እያለ ነው።ስለዚህም ቀጠለ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩእግዚአ ኩሉ ዘየሃዩ በቃሉ... ከላይ ከአርያም የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት ወይም ከላይመውረዱን አላወቁም ይሆን? እርሱስ በቃሉ ሁሉን የሚያድን ጌታ ነው።” የሰኞ ዋዜማውንይጀምራል።ይህንንም መነሻ አድርጋ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሳምንቱን ዘወረደ ብላሰይማዋለች።
ጾሙን አሁን እንዴት እንየው? “ኩኑ እንከ ከመ ብእሲ ጠቢብ... እንግዲህ ስለ ኀጢአቱ መሰረይእንደሚጾምና እንደሚጸልይ ጥበበኛ ሰው ሁኑ።መልካም ነገርን ታገኙ ዘንድ በእውነት ሂዱሰንበትን አክብሩ መልካም ነገርን ማድረግ ተማሩ… ” ሊቁ እንደሚጾምና እንደሚጸልይ ሰው ሁኑብቻ አላለም ።ነገር ግን ጾማችንን በጥበብ ይሁን ‘ጥበበኛ’ አለን እንጂ።ዳግመኛም አስተውሉ‘እንግዲህ’ ብሎ መጀመሩን ከዚህ በፊት ምንም ሁኑ ምንም በቃ ሁሉም ይብቃ ጥበብን ወደልባችሁ ጥሯት በጥበብም ጾምን እና ጸሎትን ስለ ኃጢአታችሁ ከዚህ በኋላ ገንዘብ አድርጉ።አለፍብሎ ‘እንግዲህ’ ያለውን ቃሉን ይገልጠዋል “አከለክሙ መዋዕል ዘሃለፈ ዘተቀነይክሙ ለግእዘሥጋክሙ... ለሥጋችሁ ፈቃድ የተገዛችሁበት ያለፈው ዘመን ይብቃችሁ ከእንግዲህስ ወዲህ ጹሙጸልዩም ለእግዚአብሔር ተገዙ …” አሁን ሥጋን ከምኞቱ እና ከመሻቱ ጋር እንሰቅለዋለን።ስለዚህም ከአባቱ ከቅዱስ ጴጥሮስ የተማረውን መነገር ባለበት ጊዜ ሊቁ ነገረን።”የአሕዛብን ፈቃድያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርምባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።” 1ጴጥ 4፡3 አሁን ጊዜውየጾም የመገዛት ነው።”ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፥ በረዓድም ደስ ይበላችሁ።” መዝ 2፡11ብሎ ቅዱስ ዳዊት የተናገረውን ቅዱስ ያሬድም በፍርሃት እንድንገዛ በአባቱ ቃል ይመክረናል።
ስለ ጾምም “ይህች የተከበረች እና ታላቅ ጾም ለሚያምኑ ሕዝበ ክርስቲያኖች የተሰጠች ናት ለእግዚአብሔር ልጆች መሪ የሆነቻቸው የዚችን ጾም ታላቅነት ተመልከቱ ።በዚህች ጾምየእሥራኤል ልጆች ባሕርን ተሻገሩባት፣ የዚችን ጾም ታላቅነት ተመልከቱ ዳንኤል ከአናብስት አፍዳነባት፣ የዚችን ጾም ታላቅነት ተመልከቱ ሶስና ከአይሁድ ረበናት ዳነችበት፣ የጾምን ክብሯንታላቅነቷን ተመልከቱ ታላቅነቷን ተመልከቱ ለሰነፎች ሀዘን ለጠቢባን ደስታቸው ናት፣ የጾምንታላቅነት ተመልከቱ የዚችን ጾም ” እያለ ልንጀምረው የምንደረደርለትን ጾም እያከበረ እያዜመአስታወቀን። በጾምስ እንዴት እንሁን እንዳይሉት ”እርሱ ልብ የሚል የሚያስተውል የሚጾምምራሱን ዝቅ የሚያደርግም ምስጉን ነው።በሕይወቱ ስለ ሠራው በጎ ሥራ ከአምላኩ ክፍያውንይወስዳል(የሚወስድ ነው) ” እያለ እያዜመ ይቀጥላል።”…እጄ ምድርን መሰረታት ቀኜም ሰማይንአጸና በሕይወት ትኖሩ ዘንድ በጾምና በጸሎት በቀናች ሃማኖት ወደ እኔ ተመለሱ።” ነፍሳችንበምትሰማው ሠማያዊ ዜማ የሚለን ነገር አለ። “እንጹም እንጸልይ በየዋሃትና በፍቅርለእግዚአብሔር እንሁን ቀደምት አባቶች ከኃጢአት እንደዳኑ በአርምሞ ከፈተና እንዳመለጡ(እንደሸሹ)”። ጾምን ከጸሎት አይለያትም ዋጋዋ ታላቅ ነውና።ጸሎት ደግሞ በልምድ ሳይሆንበተሰበረ ልብ በየውሃት መሆን አለበት ።አሁንም ቢሆን የውሃት ብቻውን አይበቃም።ሁሉንማሰሪያው ፍቅር ሊታከልበት ይገባል።ለዚህም ነው በዚህ ድርሰቱ ቅዱስ ያሬድ በየገጹ ቢያንስአንድ ጊዜ “አፍቅር ቢጸከ” “ወንድምህን ውደድ” የሚል ትእዛዝ ሳይጽፍ ያላለፈው።ፍቅር ያለውሰው ደግሞ በየትኛውም ጊዜ በምንም ሁኔታ ራሱን ለአምላኩ ያስገዛል፣አርምሞን ገንዘቡያደርጋል።ይህም እርሱን ወደ አላማው ያደርሰዋል።አላማው የእግዚአብሔር መሆን አይደለምን?የእርሱ ከሆነ ደግሞ ወጥመድን ፈተናን ሁሉ ያልፋል።ዓለም የምታዘጋጅለት ሁሉ ከአምላኩአይለየውም።ስለዚህ አባታችን በዚህ ፍቅር ኖሮ “ኦ ፍቁራንየ” እያለ ያዜምልናል ድምጹን እንስማ”የምወዳችሁ ወንድሞቼ የዚህ አለም ንብረት ምን ይጠቅመናል? ምድራዊ መዝገብ እንደሚጠፋአልሰማችሁምን?ስለዚህ በእግዚአብሄር መታመንን ያጸና በሕይወት ይኖራል” ይህን ያለን ደግሞንብረት አያስፈልግም ለማለት አይደለም ሁሉ እያለን እንደሌለን እንኑር ከአለም ከንቱ መጎምዠትእንጹም እያለን እንጂ።ይህ ይቻላልን? ትሉኝ ይሆናል።እኔ ምን እላችኋለሁ እርሱ ግን መልስአለው። “ይጹም ዓይን... ዓይን ይጹም ልሳን ይጹም ጆሮም ክፉ ከመስማት ይጹም በፍቅር ይህሁሉ ይሁን” ይህ ሁሉ ሲሆን ደግሞ እኛ በአለም እያለን ከአለም ውጪ እንሆናለን።ያኔ ደግሞሰማያዊ ሆንን፣ ጾምን ማለት ነው። “እስመ በጾም ወበጸሎት ይሰረይ ኩሉ ኃጢአት በጾም ድኅኑአበው ቀደምት ኤልያስ ዐርገ ውስተ ሰማያት” በጾምና በጸሎት ኃጢአት ሁሉ ይሰረያልና ፣የቀደሙአባቶች በጾም ዳኑ ኤልያስም ወደ ሰማያት ዐረገ።” ኤልያስን በጾም ሕያዋን ከመሬት ከፍ ብለውበጿሚው ሥጋቸው ሥጋዊውን ምድር አሸነፉ አለን።ስለዚህ ወገኖቼ በጾም ህግን መጠበቅ ብቻሣይሆን ከምድራዊ ሕግም በላይ በመሆን ከሥጋ ፈቃድ ወጥቶ ወደ ርቱዕ ሕይወት መሸጋገርእንዲቻል ሲያሳውቀን ነው።
እንዲህ ሊገስጸን ደግሞ ጀመረ። “አንተስ አስቀድመህ ራስህን መርምር” የምን ምርመራ ነው?ሥጋዊምርመራ አይደለም የነፍስ ህመምን እንጂ ።ወገኖቼ የጾምን በር ሳናንኳኳ አንከፍትም። ለመግባትግን እንድንገባ ሆነን መገኘት አለብን ።ከኃጢአታችን ጋር ከበደላችን ጋር ሆነን አንገባም። ያለፈውንትተን ንስሐ ገብተን ፣ ያቀድነውን የኃጢአት ቀጠሮ ሰርዘን ራሳችንን የተገባ ካደረግን በኋላ የበሩንደውል እንጫን። አሁን ከራሳችን ጋር ከምርመራ በኋላ ታርቀናል። ቀጣዩን እርሱ ያዚምልን “ጹምለእግዚአብሔርም ተገዛ” በእውነት ዜማው ይለያል፣ ጣዕመ ዜማው አዲስ ነው።”በምሥጋና ላይእንግዳ (ወንድም) መውደድን ጨምር” ምሥጋና ላይ መውደድ ጨምሩ ማለቱ ለምን ይሆን?በትክክል የሚጾም ጾም ምሥጋና ነው።ስለዚህ በምሥጋና ጾማችን ላይ እንግዳ (ወንድም) መውደድን ጨምሩ አለን።አሁንም እንዲሁ የተፈለጠው እንጨት(ጾምን) በልጥ ፍቅር መታሰር አለበትና ወንድማችሁን ውደዱ እያለ ሊቁ ያሳስበናል።
“ከምግብህ ላይ ስጥ የተራበን አጥግብ” ይህንን ዜማ ሰማችሁን? በጾም ያተረፍነውን (ቁርስ ወይምምሳ) ምግብ በምንበላ ሰአት በአይነት እንዳናካክሰው እንዲህ አለን። ያ ያልተበላ ምግብ በገንዘብየሥጋዊ ሕይወት ኢኮኖሚ ማድለቢያ ሳይሆን የነዚያ ተርበው ፍርፋሪ ያጡት እንግዶችነው።እንውደዳቸው ብሎን የለ?ታዲያ ሲርባቸው ቢያንስ በዚህ እናጥግባቸውና ፍቅራችንንየእውነት ጾማችንን የጽድቅ እናድርገው።የራባቸውን አብሉ ሳይሆን አጥግቡ ማለቱን ልብ እንበል።“ለድሃ አደጉም ፍረድ” ድሃ አደጉ ዛሬ በጾም ከእኛ የሚፈለገው የለምን?ለምኖ ስላልተሰጠውየእኛን ፍትህ አይሻምን? ለተራበው፣ለተጠማው፣ለታረዘው፣ለታመመው፣ የእኛን በጎነትለሚጠብቀው ሁሉ እንድረስ። እዝን ያለው በውሳጣዊ እዝን(ጆሮው) ይስማ። ጾማችን በረከትንያሰጠን ዘንድ ለችግረኞች ሁሉ መድረስ ቸል አንበል።
ራሳችንን መርምረን ፣ ብንጾም፣ለእግዚአብሔር እንደሚገባ ብንገዛ፣እንደ መላእክቱ ለምሥጋናብንተጋ፣ ወንድሞቻችንን እንደ ራሳችን ብንወድ፣ካለን ለተቸገሩ ብናካፍል፣ለምስኪኑ ብንራራ በኋላበተፍጻሜቱ “ይህ ለአንተ መልካም ነው” ይለናል ።
ጌታም በምሳሌ አፌን እከፍታለሁ ተብሎ በነቢዩ የተጻፈውን እንደፈጸመ ደቀ መዝሙሩም ቅዱስያሬድ የጾምን ነገር በጾሙት እየመሰለ እንዲህ አለን “ሙሴ ጾመ ዳንኤልም ጾመ ጌታም ስለ እኛጾመ ስለዚህ ጾምን ቀድሱ” ሙሴ ቢጾም ሕግን ሊቀበል ዳንኤል ቢጾም ከአናብስት አፍ ሊወጣየወገኖቹን ነፃነት ናፍቆ፣እንኪያስ ጌታ ለምን ጾመ? አርአያ ሊሆነን ፣ጾምን ሊቀድስልን እንጂ ምንጎድሎበት ምን ሊያገኝ ነው? ሁሉ በእጁ የተያዘ ነው ብሎ ቅዱስ ጴጥሮስ ነግሮን የለምን?2ኛ ጴጥ 3:10 ስለዚህ እኔም ከአባቴ ጋር አልሁ ጾምን ቀድሱ ፣ተቀድሶ ተሰጥቶናልና።ጾምን ቀድሱ ያለፈውየኃጢአት አገልግሎት ይብቃ።”ጾምን ቀድሱ ሙሴ በሲና ጾሟልና ኢያሱም በጾም ዳነ በገባኦን ፀሐይን አቆመ” ።ዜማው እንዳያልቅብን ብንጓጓም ዛሬ በነገ መቀየሩ ግድ ነውና ሳይሰናበተን “በበጎሥራ ሁሉ ስትጓዙ የሰላም መንገድን ተከተሏት በእርሷም ሂዱ ጾምን ፍፁም እንጹም የሰላም እህትቅድስት ጾምን ጌታ ራሱ ጾሟታልና ” እኛም ስንሰናበት “የማይጠልቅ ፀሐይ ፣የማይጠፋብርሐን፣የማያበድሩት ባዕለ ጸጋ ፣የሐዋርያት ጌጣቸው፣የችግረኞች ሃብታቸው፣ለተገፉትመጠጊያቸው ሁልጊዜ እናመሰግንሃለን መሀሪ ንጉሥ በሥራው ቸል የማይል።የአብርሀም የይስሐቅየያዕቆብ አምላክ ምሕረትህን አሳየን በአርአያህ የሠራኸውን የፈጠርከውን ሕዝብህን አታጥፋአትተው። ” እንዳለ ቅዱስ ያሬድ።
ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን።ይቆየን!
|